በምስራቅ ሐረርጌ ዞን የዋጋ ንረት እንዲፈጠር ዘይትና የተለያዩ የምግብ ፍጆታቸውን አከማችተው የተገኙ 197 የነጋዴ መጋዘኖች እንዲታሸጉ መደረጉን የዞኑ ንግድ ጽህፈት ቤት ገለጸ።
የጽህፈት ቤቱ ተወካይ አቶ መሐመድዚያድ ከድር እንዳሉት በዞኑ በምግብ ሸቀጦች ላይ የሚስተዋለው ህገ ወጥ ተግባር ለመከላከል የፍትህ አካላትና ህብረት ስራ ማህበራት በአባልነት የሚገኙበት ግብረ ሃይል አቋቁመው ወደ ስራ ገብተዋል።
ግብረ ሃይሉ በአንድ ሳምንት ባከናወነው እንቅስቃሴም የምግብ ፍጆታ ሸቀጦችን በድብቅ የማከማቸት እና ያልተገባ የዋጋ መጨመር ህገ ወጥ ድርጊት መታየቱን አስረድተዋል።
በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎች በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ በ197 መጋዘኖችን ውስጥ ዘይት፣ ስኳር፣ዱቄት፣ ሩዝ፣ማካሮኒንና ሌሎች የምግብ ሸቀጦች በህገ ወጥ መንገድ አካማችተው በመገኘታቸው እንዲታሸጉ መደረጉን ገልጸዋል።
በተለይ በሐረማያ ወረዳ አዴሌ ከተማ በሚገኝ 3 መጋዘኖች ውስጥ ግምቱ 30 ሚሊየን ብር የሚጠጋ ከ34ሺህ ሊትር በላይ የምግብ ዘይት፣1ሺህ 850 ኩንታል ሩዝ፣1ሺህ 450 ኩንታል ማካሮኒን፣300 ኩንታል ዱቄትና ሌሎችም የምግብ ሸቀጦች ተከማችተው ማገኘታቸውን ጠቅሰዋል።
የተሸጉ መጋዘኖች ባለቤቶች ላይ በአቃቢ ህግ በኩል ክስ በመመስረት ፍርድ ቤት በሚሰጠው ውሳኔ መሰረት እርምጃ እንደሚወሰድባቸው ያመለከቱት አቶ መሐመድዚያድ ህገ ወጥ ተግባር የመቆጣጠርና ገበያውን የማረጋጋት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
የሐረማያ ወረዳ ንግድ ጽህፈት ቤት የቁጥጥርና ኢንስፔክሽን ባለሙያ አቶ ኤልያስ ኡስማን የፍጆታ ሸቀጦችን አለአግባብ በመጋዘን ያከማቹና የተጋነነ ዋጋ በጨመሩ ነጋዴዎች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱን ኢዜአ ዘገቧል።
- ከአምስት አመት በፊት በእንጀራ እናቷ ተገደለች የተባለችው ግለሰብ በህይወት ተገኘች
by topzena1
በሰሜን ሸዋ ዞን ሞጃና ወደራ ወረዳ ከአምስት ዓመት በፊት በእንጀራ እናቷ ተገደለች የተባለችው ግለሰብ በህይወት መገኘቷ ታወቀ። ግለሰቧ መሞቷ በሀሰተኛ ምስክሮች ተረጋግጦ የእንጀራ እናቷ የ20 ዓመት እስር ቅጣት ተጥሎባቸው ነበር። ሞታለች የተባለችው ግለሰብ እና ከሳሽ የነበሩት በቁጥጥር ስር ውለዋል። የዞኑ ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ህዝብ ግንኙነት ባለሙያ ኮማንደር ደበበ […]
- “ሌሎች ህወሃቶችና ኦነግ ሸኔ ጨረሱን” የአጣዬ ነዋሪዎች ” ጅብ የሚነክሰው አናክሶ ነው ” የአቶ ምግባሩ ትንቢት
by topzena1
በክፉዎች ሴራ ቤተሰቦቻቸው፣ የአማራ ክልል፣ ኢትዮጵያና ወዳጆቻቸው ያጡዋቸው አቶ ምግባሩ ከበደና ባልደረቦቻቸው የሚረሱ እንዳልሆኑ በሁሉም ዘንድ እምነት አለ። ዶ/ር አምባቸው መኮንን፣ የክልሉ ጠቅላይ አቃቤ ሕግ የአቶ ምግባሩ ከበደና የርዕሰ መስተዳደሩ አማካሪ የአቶ እዘዝ ዋሴ በጁን 25 ቀን 2019 የቀብር ስነስርዓታቸው የተከናወነው በክፉዎች ሴራ መሆኑንን መላው የአማራ ሕዝብ ጠንቅቆ […]
- የአማራ ሕዝብ ከፖለቲካ ነጋዴዎች ራሱን አግልሎ በአንድነት ይቁም!! ሰሜን ሸዋ፣ ጭልጋ፣ ፍኖተ ሰላም አማራ እየተወጋ ነው
by topzena1
የክልሉ የሰላምና ሕዝብ ደኀንነት ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ ሲሳይ ዳምጤ ሲናገሩ እንደተሰማው በሰሜን ሸዋ ያለው ሁኔታ የከፋ ነው። አማራ አንድ ሆኖ መነሳት አለበት። የአካባቢውን አመራሮች የጠቀሱ የሌሎች ሚዲያዎች እንዳሉት ወራሪው ሃይል እጅግ ብዙ ነው። አሁን ስፍራው ላይ ያለው ሊቋቋመው አይችልም። አቶ ሲሳይ ” አማራ በአንድ ይቁም” ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል። […]
- “ሁሉንም ያማከለ ዴሞክራሲያዊ ስረዓተ መንግስት ካልተመሰረተ ወቅታዊና ረጅም ጊዜ ያስቆጠሩ ችግሮች ለመፍታት አስቸጋሪ ነው”
by topzena1
በኢትዮጵያ እውነተኛ ሁሉንም ያማከለ ዴሞክራሲያሲዊ ስረዓተ መንግስት ካልተመሰረተ አሁን ያሉትንና ረጅም ጊዜ ያስቆጠሩ የአገሪቱን ችግሮች ለመፍታት ከባድ ሊሆን እንደሚችል በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ምክክር ያደረጉ ምሁራን ገለጹ። ‘ኢትዮጵያዊነት’ በተሰኘ የሲቪክ ማኅበር አዘጋጅነት ምዕራባውያን በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ያያዙትን የተሳሳተ አቋም በተመለከተ በአለም አቀፍ ደረጃ የዌቢናር ውይይት እየተካሄደ ነው። በውይይቱ […]
Like this:
Like Loading...
Related