የኢዜማ 23 የፓርላማ እጩዎች እነማን ናቸው?

ኢዜማን ወክለው በአዲስ አበባ ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የሚወዳደሩት እጩዎች የታወቁ ሲሆን፤ ባልደራስ ከመኢአድና አብን ጋር በምርጫው እርስ በእርስ ላለመፎካከር ስምምነት ላይ ደርሰዋል፡፡
በዘንድሮ ምርጫ ኢዜማን ወክለው በየወረዳው ለፓርላማ ከሚወዳደሩት 23 እጩዎች መካከል የፓርቲው መሪ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ፣ የፓርቲው ም/መሪ አንዷለም አራጌ፣ አቶ ግርማ ሰይፉ፣ የኢኮኖሚ ምሁሩ ፕ/ር በፈቃዱ ደግፌና አርክቴክት ዮሐንስ መኮንን ተጠቃሽ ናቸው።
ፓርቲውን ወክለው ለፓርላማ የሚወዳደሩ 23 እጩዎች በየወረዳው ሲደላደሉም፣ ምርጫ ወረዳ 1/9 አርክቴክት ዮሐንስ መኮንን፣ ምርጫ ወረዳ 2/14 አቶ ደረጀ ተክሌ፣ ምርጫ ወረዳ 3 ዶ/ር ጥላሁን ገብረ ሕይወት፣ ምርጫ ወረዳ 4 አቶ ተክሌ በቀለ፣ ምርጫ ወረዳ 5 አቶ አበበ ተሻለ፣ ምርጫ ወረዳ 6 አቶ ግርማ ሰይፉ፣ ምርጫ ወረዳ 7 ወ/ት ናርዶስ ስለሺ፣ ምርጫ ወረዳ 8 ከውሰር ኢድሪስ፣ ምርጫ ወረዳ 10 አቶ ዘላለም ወርቅአገኘሁ፣ ምርጫ ወረዳ 11 አቶ የጁ አልጋው ጀመረ፣ ምርጫ ወረዳ 12/13 አቶ አንዷለም አራጌ፣ ምርጫ ወረዳ 15 ዶ/ር በላይ እጅጉ፣  ምርጫ ወረዳ 16  ዶ/ር አንማው አንተነህ፣ ምርጫ ወረዳ 17 ዶ/ር ዳዊት አባተ፣ ምርጫ ወረዳ 18  አቶ ወንድወሰን ተሾመ፣ ምርጫ ወረዳ 19 አቶ በላይ ደስታ፣ ምርጫ ወረዳ 20  አቶ ባንትይገኝ ደስታ፣ ምርጫ ወረዳ 21/22  አቶ ብርሃኑ ወልደ ጊዮርጊስ፣ ምርጫ ወረዳ 23  ፕ/ር ብርሀኑ ነጋ፣ ወረዳ 24 ፕ/ር በፍቃዱ ደግፌ፣ ምርጫ ወረዳ 25 አቶ እንዳልካቸው ፈቃደ፣ ምርጫ ወረዳ 26/27 ዶ/ር መለስ ገብረጊዮርጊስ፣ ምርጫ ወረዳ 28  ዶ/ር ባንትይገኝ ታምራት መሆናቸው ታውቋል።
አዲስ አበባ ላይ ጠንካራ ተፎካካሪ ይሆናል ተብሎ የሚጠበቀው ኢዜማ፤ ለአዲስ አበባ ምክር ቤት ካቀረባቸው 138 እጩዎች መካከል ታዋቂው የኢኮኖሚ ተንታኝና የፓን አፍሪካ ንግድ ም/ቤት ፕሬዚዳንት፣ አቶ ክቡር ገና  ተጠቃሽ ናቸው።
አዲስ አበባ ራሷን የቻለች ክልል መሆን አለባት በሚል የሚሟገተውና በእስር ላይ በሚገኘው አቶ እስክንድር ነጋ የሚመራው ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ በበኩሉ፤ ለአዲስ አበባ ም/ቤት 138 እንዲሁም ለፓርላማ 23 እጩዎች ማዘጋጀቱን ገልጾ፣ዝርዝራቸውን ከሰሞኑ ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግም አስታውቋል።
ባልደራስ፤ ከመኢአድና አብን ጋር እርስ በእርስ ባለመፎካከር፣ በአንጻሩ በምርጫው  በትብብር  ለመስራት የፓለቲካ ስምምነት ላይ  መድረሳቸውን  የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል። በዚህም መሰረት ባልደራስ እጩ ባቀረበባቸው ወረዳዎች የአብንና የመኢአድ ድርሻ ድጋፍ መስጠት ሲሆን፤ ባልደራስ በማይወዳደርባቸውና አብንና መኢአድ በሚወዳደሩባቸው አካባቢዎች ደግሞ ባልደራስ ትብብርና ድጋፍ እንደሚያደርግ ሃላፊው አብራርተዋል፡፡

  • የተጠልፈቸው ጸጋ በላቸው ነጻ ሆነች፤ ጠላፊው አልተያዘም
    ወይዘሪት ፀጋ በላቸውን ከተጠርጣሪው ግለሰብ ማስጣል መቻሉን የሲዳማ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ አስታወቀ። የሲዳማ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሃላፊ አቶ አለማየሁ ጢሞቲዮስ ጉዳዩን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ በተደረገው የተቀናጀ የፀጥታ ኦፕሬሽን በተጠርጣሪው ግለሰብ የተጠለፈችውን ወይዘሪት ፀጋ በላቸውን ማስጣል መቻሉን ተናግረዋል። ግንቦት 15 ቀን 2015 ከመደበኛ ስራዋ ወጥታ ወደቤቷ ስታቀና ተጠርጣሪው ግለሰብContinue Reading
  • ፌደራል ፖሊስ ሆን ብለው ሐሰተኛ መረጃ በሚያሰራጩ አካላት ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል አለ
    ሆን ብለው ሕብረተሰቡን ለማሳሳት ሐሰተኛ መረጃ በሚያሰራጩ ግለሰቦች ላይ እየወሰደ ያለውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታወቀ። ተቋሙ አገራዊ ለውጡን ተከትሎ መንግስት ለህዝብ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ከወሰዳቸው እርምጃዎች መካከል የሰብአዊ መብት ጥሰት ይፈፀምበት የነበረውን ማዕከላዊ የወንጀል ምርመራን መዝጋት መሆኑንና ይሄንን ተከትሎ በፖሊስ የወንጀል ምርመራ ስራ ላይ ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበትContinue Reading
  • ኢሰመኮ ሁለት ሰዎች ሲሞቱ በርካቶች የጸጥታ ሃይሎችን ጨምሮ ጉዳት እንደደረሰባቸው አስታወቀ
    በሸገር ከተማ ከመስጊዶች መፍረስ ጋር ተያይዞ የተነሱ ተቃውሞዎችን እና የደረሰ ጉዳትን በተመለከተ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከግንቦት 18 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ በተለይም በአዲስ አበባ አንዋር መስጊድ ውስጥ እና በተወሰኑ አካባቢዎች በሸገር ከተማ በመንግሥት አካላት ከፈረሱ መስጊዶች ጉዳይ ጋር ተያይዞ የተነሱ ተቃውሞዎችን ተከትሎ የደረሰውን የሰዎች ሞት እና ጉዳቶችን በተመለከተContinue Reading
  • አዲስ አበባና በሸገር ከተሞች የፈረሱትን ቤቶችና ማህበራዊ ቀውስ አስመልክቶ ኢሰመኮ መገለጫ አወጣ
    በአዲስ አበባ እና በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተሞች እየተካሄደ ነው ባለው የቤት ፈረሳ እና የግዳጅ የማስነሳት ሂደት 111 ሺህ 811 ቤቶች መፍረሳቸውን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) አስታወቀ። ኢሰመጉ ይህንን የገለጸው ከጥቅምት 2015 ዓ.ም. ጀምሮ በጉዳዩ ላይ ያካሄደውን የምርመራ ሪፖርት ግንቦት 23/2015 ዓ.ም. ይፋ ባደረገበት ጊዜ ነው። ኮሚሽኑ ይህንን አሃዝ ይፋContinue Reading
See also  የኢትዮጵያ ጦር ከላይሊበላ ወደ ሰቆጣ እየገሰገሰ ነው፤ ትህነግ " ወደ መቀለ እንዳይገቡ አስጥሉኝ" አለ

Leave a Reply