በትግራይ አምስት ፋብሪካዎች በሙሉ አቅማቸው ማምረት ጀመሩ፣ አንዱ ኤክስፖርት ጀምሯል

የመልሶ ማቋቋሙ አንድ አካል የሆነው ስራ በስኬት እየተከናወነ መሆኑንን ከሚያመልክቱት ተጋሮች አንዱ የፋብሪካዎች መልሶ ስራ ማስጀመር መሆኑ ይታመናል። በመሆኑም በትግራይ አምስት ፋብሪካዎች ስራ መጀመራቸውና አንደናው ደግሞ ኤክስፖርት መጀመሩ ተመልክቷል።  ይህ የተገለጸው በሰላም ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል ሰብሳቢነት የሚመራው የብሄራዊ ድንገተኛ አደጋ አስተባባሪ ማዕከል የሚኒስትሮች ኮሚቴ ሳምንታዊ መደበኛ ስብሰባውን ባካሄድበት ወቅት ነው።

በስበሰባው የኮሚቴው አባል ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች በትግራይ ክልል እና በመተከል ዞን በማድረግ ላይ ስላሉት የአስቸኳይ እርዳታ አቅርቦትና ስርጭት ሚኒስትሯ ሪፖርት አቅርበዋል፡፡ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶቹ ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ጋር በመቀናጀት ምግብና ምግብ ነክ ያልሆኑ አቅርቦቶችን በተቀናጀና በተጠናከረ መልኩ እያቀረቡ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ከጊዜያዊ የእርዳታ አቅርቦት ባሻገር ህዝቡን በቋሚነት መልሶ የማቋቋምና ወደ መደበኛ ህይወት የመመለስ ስራ በተጓዳኝ እየተካሄደ መሆኑንም አረጋግጠዋል፡፡

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ተወካዮች የዕርዳታ ስርጭቱና ክፍፍሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ ከፍ እያለ መምጣቱን አረጋግጠዋል፡፡  በክልሉ ያለው አጠቃላይ ሁኔታም እየተሻሻለ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም በአሁኑ ወቅት አምስት ፋብሪካዎች በሙሉ አቅማቸው ስራ መጀመራቸውን እና ከእነዚህ አምስት ፋብሪካዎች ውስጥ አንዱ ለውጭ ገበያ አቅርቦት መጀመሩን መናገራቸውን ከሰላም ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ዝግጅት ክፍላችን ያናገራቸው የትግራይ ተወላጆች እንዳሉት አሁን መርጋጋትና ነገሮች ወደነበሩበት እየተመለሱ ነው። ዋናው ችግሩ የሚዲያው ፕሮፓጋንዳ ነው ብለዋል። አያይዘውም እርቅ ላይ ቢተኮር እንደሚሻል ጠቁመዋል።

  • የተጠልፈቸው ጸጋ በላቸው ነጻ ሆነች፤ ጠላፊው አልተያዘም
    ወይዘሪት ፀጋ በላቸውን ከተጠርጣሪው ግለሰብ ማስጣል መቻሉን የሲዳማ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ አስታወቀ። የሲዳማ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሃላፊ አቶ አለማየሁ ጢሞቲዮስ ጉዳዩን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ በተደረገው የተቀናጀ የፀጥታ ኦፕሬሽን በተጠርጣሪው ግለሰብ የተጠለፈችውን ወይዘሪት ፀጋ በላቸውን ማስጣል መቻሉን ተናግረዋል። ግንቦት 15 ቀን 2015 ከመደበኛ ስራዋ ወጥታ ወደቤቷ ስታቀና ተጠርጣሪው ግለሰብContinue Reading
  • ፌደራል ፖሊስ ሆን ብለው ሐሰተኛ መረጃ በሚያሰራጩ አካላት ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል አለ
    ሆን ብለው ሕብረተሰቡን ለማሳሳት ሐሰተኛ መረጃ በሚያሰራጩ ግለሰቦች ላይ እየወሰደ ያለውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታወቀ። ተቋሙ አገራዊ ለውጡን ተከትሎ መንግስት ለህዝብ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ከወሰዳቸው እርምጃዎች መካከል የሰብአዊ መብት ጥሰት ይፈፀምበት የነበረውን ማዕከላዊ የወንጀል ምርመራን መዝጋት መሆኑንና ይሄንን ተከትሎ በፖሊስ የወንጀል ምርመራ ስራ ላይ ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበትContinue Reading
  • ኢሰመኮ ሁለት ሰዎች ሲሞቱ በርካቶች የጸጥታ ሃይሎችን ጨምሮ ጉዳት እንደደረሰባቸው አስታወቀ
    በሸገር ከተማ ከመስጊዶች መፍረስ ጋር ተያይዞ የተነሱ ተቃውሞዎችን እና የደረሰ ጉዳትን በተመለከተ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከግንቦት 18 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ በተለይም በአዲስ አበባ አንዋር መስጊድ ውስጥ እና በተወሰኑ አካባቢዎች በሸገር ከተማ በመንግሥት አካላት ከፈረሱ መስጊዶች ጉዳይ ጋር ተያይዞ የተነሱ ተቃውሞዎችን ተከትሎ የደረሰውን የሰዎች ሞት እና ጉዳቶችን በተመለከተContinue Reading
  • አዲስ አበባና በሸገር ከተሞች የፈረሱትን ቤቶችና ማህበራዊ ቀውስ አስመልክቶ ኢሰመኮ መገለጫ አወጣ
    በአዲስ አበባ እና በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተሞች እየተካሄደ ነው ባለው የቤት ፈረሳ እና የግዳጅ የማስነሳት ሂደት 111 ሺህ 811 ቤቶች መፍረሳቸውን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) አስታወቀ። ኢሰመጉ ይህንን የገለጸው ከጥቅምት 2015 ዓ.ም. ጀምሮ በጉዳዩ ላይ ያካሄደውን የምርመራ ሪፖርት ግንቦት 23/2015 ዓ.ም. ይፋ ባደረገበት ጊዜ ነው። ኮሚሽኑ ይህንን አሃዝ ይፋContinue Reading
See also  እስራኤል አልጃዚራ ቴሊቪዥን፣ አሶሲየትድ ፕሬስና ሌሎች ሚዲያዎች የሚጠቀሙበትን ህንጻ አወደመች

Leave a Reply