አሜሪካ የሰባ ሁለት ሰዓት ጊዜ ገደብ ሰጠች የሚባለውን መንግስት አያውቀውም

ትህነግ ከፍተኛ ሃብት ያፈስላቸዋል የሚባሉት ነጭ የሚዲያ ሰዎች አሜሪካ ለኢትዮጵያ ማስጠንቀቂያ ሰጥች በሚል በስፋት እያሰራጩት ስላለው ዜና ኢትዮጵያ የምታውቀው ነገር እንደሌለ ተገለጸ። ዜናውም ፈጠራ እንደሆነ ተጠቆመ። ይልቁኑም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ ለመግባት መሞከሩ ጥያቄ የሚያስነሳ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።

እነ ማርቲን ፓላውት ” ሰዓቱ ደረሰ” በሚል ኢትዮጵያ የአማራ ላዩ ሃይልና የኤርትራን ወታደሮች ከትግራይ እንድታሰወጣ የአሜሪካ ውጭጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን በስልክ ለጠቅላይ ሚኒስትር አብይ መመሪያ መስጠታቸውንና መመሪያውም ተግባራዊ የሚሆነው ማምሻውን እንደሆነ በቲውተር ገሳጻቸው ሲያሰራጩና ውዳሴ ዚጎርፍላቸው ነበር የዋሉት።
ፋክት ቼክ የአሜሪካን ኤንባሲን፣ የመንግስት ባለስልጣን አነጋግሮ ይፋ እንዳደረገው ዜናው ፈጠራ ወይም ሃሰት መሆኑንን አመልክቷል። ዝርዝሩንም እንደሚከተለው አትሟል። ከታች ይነበባል።

በርካታ የማህበራዊ ሚድያ ተጠቃሚዎች፣ የቀጠናው ተንታኞች እንዲሁም አክቲቪስቶች የዛሬ ሳምንት ማክሰኞ እለት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እና የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ቢሮ ሀላፊ አንቶኒ ብሊንከን በስልክ ያረጉትን ውይይት ተከትሎ “አሜሪካ የኤርትራ እና የአማራ ሀይሎች ከትግራይ ክልል እንዲወጡ የ72 ሰአት ግዜ ሰጥታለች” የሚል መረጃ ሲያሰራጩ ነበር።

እነዚህ አካላት ጨምረውም ይህ የ72 ሰአት ግዜ ካልተከበረ ኢትዮጵያ ላይ ማእቀብ እንደሚጣል ሲያትቱ እና ሲገምቱ ነበር። ኢትዮጵያ ቼክ በዚህ ዙርያ ከአሜሪካ እንዲሁም ኢትዮጵያ መንግስታት መረጃ ጠይቋል።

ከአሜሪካ መንግስት በኢሜይል ያገኘነው መረጃ እንደሚጠቁመው እንዲሁም በተለያዩ ሚድያዎች ባሳለፍነው ሳምንት እንደተዘገበው አንቶኒ ብሊንከን “የውጪ ሀይሎች” ብለው የገለጿቸው የኤርትራ እና የአማራ ሀይሎች ክልሉን ለቀው እንዲወጡ ጠይቀዋል። ያገኘነው መረጃ ግን ከዚህ ውጪ “72 ሰአት” ተብሎ የተቀመጠ ነገር እንዳልነበር ይጠቁማል። ከኢትዮጵያ መንግስት በኩል ያናገርናቸው አንድ ባለስልጣንም “እንዲህ አይነት ነገር እንደተባለ መረጃ የለኝም” ብለው ለኢትዮጵያ ቼክ አጭር መልስ ሰጥተዋል።

ሌላኛው ያናገርናቸው የፖለቲካ ተንታኝ ደግሞ “72 ሰአት ተብሎ በአሜሪካ ተቀምጦ ቢሆን ኖሮ ውጭ ጉዳይ ቢሯቸው ማክሰኞ ያወጣው መግለጫ ላይ እናየው ነበር፣ ያ ግን አልሆነም። ያ ለምን አልሆነም ሲባል መቼም አሜሪካ መግለጫዋ ላይ ለማስፈር ሳትደፍር ቀርታ አይመስለኝም፣ ጭራሽ ያልተባለ ነገር ስለሆነ እንጂ” ብለዋል። የኢትዮጵያ ቼክ ማጣራት እንደሚጠቁመው ይህ ተሰጠ የተባለ የ72 ሰአት ግዜ የተሳሳተ መረጃ ነው።

See also  የዓለም ምግብ ፕሮግራም የተቀመጠለትን መስፈርት አክብሮ ከአዲስ አበባ ወደ መቀሌ የመጀመሪያ በረራ አደረገ

በተያያዘ ሌላ ዜና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ ለመግባት መሞከሩ ጥያቄ የሚያስነሳ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በዛሬው እለት በሰጡት ሳምንታዊ መግለጫ፥ ሱዳን ድንበር ጥሳ መግባቷን ኢትዮጵያ በግልጽ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ባሳወቀችበት ወቅት በጉዳዩ ላይ አንድም ነገር አለማለቱን ነው የጠቀሱት፡፡

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት አሁን ላይ በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ ለመግባትና በትግራይ ክልል ስላለው ወቅታዊ ሁኔታና የሰብዓዊ ድጋፍ አስመልክቶ ልዩ ትኩረት እንደሰጠው አድርጎ ለማስመሰል የሚጥርበት ሁኔታ ትክክል አይደለም ብለዋል አምባሳደር ዲና፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃም ተቀባይነት የለውም ብለዋል፡፡ የድንበር ሁኔታውን በመተው በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ ለመግባት የሚያደርገው ጥረትም በዓለም ላይ ትልቅ ጥያቄ የሚያጭር ነው ማለታቸውን የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት አመልክቷል።

  • የተጠልፈቸው ጸጋ በላቸው ነጻ ሆነች፤ ጠላፊው አልተያዘም
    ወይዘሪት ፀጋ በላቸውን ከተጠርጣሪው ግለሰብ ማስጣል መቻሉን የሲዳማ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ አስታወቀ። የሲዳማ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሃላፊ አቶ አለማየሁ ጢሞቲዮስ ጉዳዩን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ በተደረገው የተቀናጀ የፀጥታ ኦፕሬሽን በተጠርጣሪው ግለሰብ የተጠለፈችውን ወይዘሪት ፀጋ በላቸውን ማስጣል መቻሉን ተናግረዋል። ግንቦት 15 ቀን 2015 ከመደበኛ ስራዋ ወጥታ ወደቤቷ ስታቀና ተጠርጣሪው ግለሰብContinue Reading
  • ፌደራል ፖሊስ ሆን ብለው ሐሰተኛ መረጃ በሚያሰራጩ አካላት ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል አለ
    ሆን ብለው ሕብረተሰቡን ለማሳሳት ሐሰተኛ መረጃ በሚያሰራጩ ግለሰቦች ላይ እየወሰደ ያለውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታወቀ። ተቋሙ አገራዊ ለውጡን ተከትሎ መንግስት ለህዝብ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ከወሰዳቸው እርምጃዎች መካከል የሰብአዊ መብት ጥሰት ይፈፀምበት የነበረውን ማዕከላዊ የወንጀል ምርመራን መዝጋት መሆኑንና ይሄንን ተከትሎ በፖሊስ የወንጀል ምርመራ ስራ ላይ ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበትContinue Reading
  • ኢሰመኮ ሁለት ሰዎች ሲሞቱ በርካቶች የጸጥታ ሃይሎችን ጨምሮ ጉዳት እንደደረሰባቸው አስታወቀ
    በሸገር ከተማ ከመስጊዶች መፍረስ ጋር ተያይዞ የተነሱ ተቃውሞዎችን እና የደረሰ ጉዳትን በተመለከተ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከግንቦት 18 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ በተለይም በአዲስ አበባ አንዋር መስጊድ ውስጥ እና በተወሰኑ አካባቢዎች በሸገር ከተማ በመንግሥት አካላት ከፈረሱ መስጊዶች ጉዳይ ጋር ተያይዞ የተነሱ ተቃውሞዎችን ተከትሎ የደረሰውን የሰዎች ሞት እና ጉዳቶችን በተመለከተContinue Reading
  • አዲስ አበባና በሸገር ከተሞች የፈረሱትን ቤቶችና ማህበራዊ ቀውስ አስመልክቶ ኢሰመኮ መገለጫ አወጣ
    በአዲስ አበባ እና በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተሞች እየተካሄደ ነው ባለው የቤት ፈረሳ እና የግዳጅ የማስነሳት ሂደት 111 ሺህ 811 ቤቶች መፍረሳቸውን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) አስታወቀ። ኢሰመጉ ይህንን የገለጸው ከጥቅምት 2015 ዓ.ም. ጀምሮ በጉዳዩ ላይ ያካሄደውን የምርመራ ሪፖርት ግንቦት 23/2015 ዓ.ም. ይፋ ባደረገበት ጊዜ ነው። ኮሚሽኑ ይህንን አሃዝ ይፋContinue Reading
  • አባ መልዓከ ሰላም ምስክርነት ሰጡ – የኤሊያስ ወረዳ አስተዳዳሪ ” ተማርከዋል፣ አብቅቷል” አሉ
    ላለፉት አምስት ቀናት በከፍተኛ ደረጃ መነጋገሪያ የሆነውና የፌደራልና የክልል መንግስት ምንም መረጃ ያልሰጡበት የደብረ ኤሊያስ ገዳም በርካቶችን አስጨንቆ ከርሟል። ገዳማቱ ወታደራዊ ማስለጠኛ፣ የሚፈለጉ ሰዎች መመሸጊያና የወንጀለኞች መከማቻ እንደሆነ ቢገለጽም፣ ይህን የማይቀበሉ አባባሉን ሲኮንኑ ከርመዋል። “ግራኝ አብይ አህመድ” በሚል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገዳማት እንዲወድሙ መመሪያ እንደሰጡ ተደርጎ በስፋትና በቅብብሎሽ የተሰራጨው ዜና “ኦሮሞንContinue Reading

Leave a Reply