የህወሓት ጁንታ በሰው ልጅ ላይ ሊፈጸም የማይችል ግፍ ፈጽሞብናል – የሰሜን ዕዝ አባላት

“ጽንፈኛው የህውሓት ጁንታ በሰው ልጅ ላይ ሊፈጸም የማይችል ግፍ ፈጽሞብናል” ሲሉ በህክምና ላይ የሚገኙ የሰሜን ዕዝ አባላት ተናገሩ። ምክትል መቶ አለቃ ዳዊት ደርቤ “በወገን ጥቃት ይደርስብናል ብለን ባለሰብንበት ወቅት በሌሊት በመጥረቢያ እጄ ተቆረጠ” ይላል። “ሞቷል ብለው ትተውኝ ስለሄዱ ተረፍኩ፤ ሌሎች የሰራዊቱ አባላት ግን በአሰቃቂ ሁኔታ ተገደሉ” ሲል ይገልጻል።

“ጁንታው በሰራዊቱ ላይ የፈጸመው ግፍ በጽኑ መወገዝ ያለበት ድርጊት ነው” የሚለው ተጎጂው፤ “በወገን ላይ ቀርቶ በጠላት ላይ ሊፈጸም የማይገባ ግፍ ነው” ብሏል። ሌላው የሰራዊቱ አባል ሻለቃ ባሊና ሰሚ ተመሳሳይ ጥቃት እንደደረሰበት ይናገራል። “ሰራዊቱ የክልሉን ህዝብ በተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ሲያግዝ ቆይቶ ቢሆንም ለውለታው የተከፈለው አሰቃቂና አሳዛኝ ግፍ ነው” ብለዋል።

ቡድኑ በሰራዊቱ አባላት ላይ ከፈጸመው በደል በተጨማሪ በሰሜን ዕዝ ውስጥ የሚገኘው የመቀሌ መከላከያ ሶስተኛ ደረጃ ሆስፒታልን ጨምሮ የሰራዊቱ የተለያዩ ንብረቶችን እንዳወደመ ጠቁመዋል።

ሆስፒታሉ ጉዳት ሳይደርስበት በፊት ለሰራዊቱ፣ ለሰራዊቱ ቤተሰቦችና እና ለአካባቢው ነዋሪዎች እስከ ቀዶ ህክምና ድረስ አገልግሎት እንደሚሰጥ ጠቁመው፤ “ጁንታው ሆስፒታሉን ሙሉ በሙሉ በመዝረፍና በማውደም ለህዝብ ያለውን ንቀት በተግባር አሳይቷል” ብለዋል።

ሻለቃ ዶክተር ከበደ አደለ

በመቀሌ የመከላከያ ሶስተኛ ደረጃ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ሻለቃ ዶክተር ከበደ አደለ የሆስፒታሉ ንብረት ሙሉ በሙሉ በጁንታው መውደሙን አረጋግጠዋል። “ሆስፒታሉ 160 አልጋዎች ያሉት ሲሆን ከመከላከያ ሰራዊት በተጨማሪ ለዜጎች አገልግሎት እየሰጠ ነበር” ያሉት ሜዲካል ዳይሬክተሩ፤ መንግስት አስፈላጊውን ቁሳቁስ በማሟላት ሆስፒታሉን ወደ ስራ መመለሱን ገልጸዋል።  (ኢዜአ)

  • የተጠልፈቸው ጸጋ በላቸው ነጻ ሆነች፤ ጠላፊው አልተያዘም
    ወይዘሪት ፀጋ በላቸውን ከተጠርጣሪው ግለሰብ ማስጣል መቻሉን የሲዳማ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ አስታወቀ። የሲዳማ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሃላፊ አቶ አለማየሁ ጢሞቲዮስ ጉዳዩን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ በተደረገው የተቀናጀ የፀጥታ ኦፕሬሽን በተጠርጣሪው ግለሰብ የተጠለፈችውን ወይዘሪት ፀጋ በላቸውን ማስጣል መቻሉን ተናግረዋል። ግንቦት 15 ቀን 2015 ከመደበኛ ስራዋ ወጥታ ወደቤቷ ስታቀና ተጠርጣሪው ግለሰብContinue Reading
  • ፌደራል ፖሊስ ሆን ብለው ሐሰተኛ መረጃ በሚያሰራጩ አካላት ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል አለ
    ሆን ብለው ሕብረተሰቡን ለማሳሳት ሐሰተኛ መረጃ በሚያሰራጩ ግለሰቦች ላይ እየወሰደ ያለውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታወቀ። ተቋሙ አገራዊ ለውጡን ተከትሎ መንግስት ለህዝብ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ከወሰዳቸው እርምጃዎች መካከል የሰብአዊ መብት ጥሰት ይፈፀምበት የነበረውን ማዕከላዊ የወንጀል ምርመራን መዝጋት መሆኑንና ይሄንን ተከትሎ በፖሊስ የወንጀል ምርመራ ስራ ላይ ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበትContinue Reading
  • ኢሰመኮ ሁለት ሰዎች ሲሞቱ በርካቶች የጸጥታ ሃይሎችን ጨምሮ ጉዳት እንደደረሰባቸው አስታወቀ
    በሸገር ከተማ ከመስጊዶች መፍረስ ጋር ተያይዞ የተነሱ ተቃውሞዎችን እና የደረሰ ጉዳትን በተመለከተ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከግንቦት 18 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ በተለይም በአዲስ አበባ አንዋር መስጊድ ውስጥ እና በተወሰኑ አካባቢዎች በሸገር ከተማ በመንግሥት አካላት ከፈረሱ መስጊዶች ጉዳይ ጋር ተያይዞ የተነሱ ተቃውሞዎችን ተከትሎ የደረሰውን የሰዎች ሞት እና ጉዳቶችን በተመለከተContinue Reading
  • አዲስ አበባና በሸገር ከተሞች የፈረሱትን ቤቶችና ማህበራዊ ቀውስ አስመልክቶ ኢሰመኮ መገለጫ አወጣ
    በአዲስ አበባ እና በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተሞች እየተካሄደ ነው ባለው የቤት ፈረሳ እና የግዳጅ የማስነሳት ሂደት 111 ሺህ 811 ቤቶች መፍረሳቸውን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) አስታወቀ። ኢሰመጉ ይህንን የገለጸው ከጥቅምት 2015 ዓ.ም. ጀምሮ በጉዳዩ ላይ ያካሄደውን የምርመራ ሪፖርት ግንቦት 23/2015 ዓ.ም. ይፋ ባደረገበት ጊዜ ነው። ኮሚሽኑ ይህንን አሃዝ ይፋContinue Reading
See also  ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

1 Comment

  1. ህወሀት ሆስፒታል አወደመ?
    ህወሀት የትግራይን ክልል ህዝብን በኢኮኖሚ እና በማህበራዊ ህይወት ያገዘ የወገኑን ሰው እጅ በመጥረቢያ ቆርጦ እና ሌሎችን በተመሳሳይ መልክ በክልሉ በማገዝ ይኖሩ የነበሩትን የኢትዮጵያ መከላከያ አባላትን ንብረት እያወደመ በአሰቃቂ መልክ ገደለ?

    ይህ አሰቃቂ ድርጊት እንኳን ከህወሀት ቀርቶ ከማንም አረመኔ ጠላት አይጠበቅም።

Leave a Reply