የወ/ሮ አዜብ መስፍን የቀድሞ ባለቤት አገር ከዱ፤ በኢትዮጵያ ስም ለፓርቲያቸው ይሰሩ ነበር

ትህነግን በጉያቸው ይዘው በመንግስት ስም የዲፕሎማሲ ትንቅንቅ እንደሚያደርጉ ሲናገሩ የነበሩት ዲፕሎማት አገር መክዳታቸውን በገሃድ እስከተናገሩበት ቀን ድረስ ለትህነግ ይሰሩ እንደነበር የአሜሪካ ዲፕሎማት ለኢትዮ 12 የአሜሪካ ተባባሪ ጠቆሙ። የሰውየው ሹመት መንግስት ራሱን በራሱ ሲያርድ እንደነበር ማሳያ ነው ተብሏል።

የቀድሞ የወይዘሮ አዜብ ባለቤት የነበሩት አቶ ብርሃነ ኪዳና ማሪያም ከትህነግ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልነታቸው የተባረሩት በሜይ 2016 ነበር። የቀድሞ ባለቤታቸው ስብሰባ ረግጠው ክትህነግ ስራ አስፈጻሚነት ስልጣንና ከኤፈርት ስራ አስኪያጅነታቸው ሲባረሩ ቆንስላ የሆኑት አቶ ብርሃነ በመቸረሻ አካባቢ ከአቶ ስብሃት ጋር ከመጋጨታቸው ውጪ የትህነግ ታማኝ አገልጋይ እንደነበሩ በቅርብ የሚያውቋቸው ይነገራሉ። ሃብታም መሆናቸውንም ያውቃሉ።

አቶ ብርሃነ “በትግራይ ክልል እየተፈጸመ ያለው የዘር ማጥፋት ጦርነት እና መንግሥት በሌሎችም የኢትዮጵያ አካባቢዎች የሚያደርሰውን ጭቆናና ውድመት ተቃውሜ ነው” ሲሉ አገር መክዳታቸው ይፋ ሲያደርጉ በተመሳሳይ ሰዓት ኢትዮጵያዊያን በአንድነት የአሜሪካን ጣልቃ ገብነት ሊያወገዙ አደባባይ ወጥተው ነበር።

Related stories   UNDP Memo Echoes Ethiopian Talking Points on Tigray

በአሜሪካን የሰልፍ ታሪክ እጅግ ሰፊ ቁጥር ያላቸው ኢትዮጵያዊያን ትህነግ በሃሰት መረጃ የሚከፈላቸውን ዲፕሎማቶችና ሚዲያዎች በመጠቀም ዓለምን እያሳተ እንደሆን በአንድነት በሚያስተጋቡበት ወቅት ዜናውን ለማስቀየር የተመረጠ ጊዜ ጥብቀው አገር መክዳታቸውን ይፋ እንዳደረጉ ነው ዲፕሎማቱ የገለጹት።

በኤምባሲ ደረጃ ባሉ ግንኙነቶች ለተሳሳቱ መረጃዎች ኢትዮጵያን ወክለው እንደ እውነት በመቀበል ስማቸው እንዳይጠቀስ እየጠየቁ መረጃ ይሰጡ እንደነበር ዲፕሎማቱ አመልክተዋል።

አሜሪካ ካሉ የትህነግ ነባር አባላት ጋር ግንኙነት የሚያደርጉት አቶ ብረሃነ አገር መክዳታቸውን ይፋ እስካደረጉበት ሰዓት ድረስ በተሰጣቸው ሃላፊነት አማካይነት ከዓለም አቀፍ ተቋማትና ድርጅቶች፣ እንዲሁም አገሮች ጋር ትህነግ ለከፈተው የቅጥፈት ዘመቻ ደጋፊ ስራ ሲሰሩ እንደነበር መንግስት በማወቁ ከሳምንት በፊት ታግደው እንደነበር ምንጩ አመልክተዋል።

Related stories   

የትህነግ ታሳሪዎች – ከበረሃ ከተማረኩ ጀምሮ ሰብአዊ እንክብካቤ እየተደረገላቸው መሆኑንን፣ ሲያዙ ተኩስና ማስፈራራት እንደነበር ገለጹ

እግዱ ጸንቶ ደብዳቤ ሳይደርሳቸው አስቀድመው በግጥምጥሞሽ በተመረጠ ቀን የክህደት ደብዳቤ በማሰራጨት ወደ ድርጅታቸው ዓላማ አስፈጻሚነት መዛወራቸውን ይፋ ያደረጉት አቶ ብርሃነ ከዚህ ቀደም ሲያገለግሉ ከነበሩባቸው ቁልፍ የሚዲያና የንግድ ሞኖፖሊ ተቋም አሃአልፊነታቸው አንጻር በኢትዮጵያ መለያ ለትህነግ ሲጫወቱ መቆየታቸው አስገራሚ እንዳልሆነ ዜናውን የሰሙ ገልጸዋል። እነደውም ዜናው መንግስት እሳቸውን በዚህ ከፈተኛ ቦታ ላይ አስቀምጦ ራሱን ሲያርድ መቆየቱ እንደሆነም ተመክቷል።

See also  ጋይንት ከአሸባሪው ቡድን ነጻ ሆነ!

አቶ ብርሃነ ኪዳነ ማርያም የዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ሃላፊ ነበሩ፤ የኢትዮጵያ ብሮድካስት ኮርፖሬሽን ዋና ዳይሬክተር ሆነው ሰርተዋል። ከአቶ አሰፋ ማሞ ሞት በሁዋላ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴን መርተዋል። የትህነግን ታላቅ የንግድ ተቋም ኤፈርትን ከቀድሞ ሚስታቸው ወ/ሮ አዜብ ስር ሆነው በስራ አስኪያጅነት አስተዳድረዋል።

ኪዳነ ማርያም ማህረት በሚል ስያሜ የሚታወቁት እኚህ ሰው ከትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግንባር ስራ አስፈጻሚነት ሲበረሩ በሎሳንጅለስ የኢትዮጵያ ቆንስላ ሆነው ተመድበዋል። ወዲያው ለውጡ ተጣድፎ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ ወደ መሪነት እንደመጡ አቶ ካሳ ከዋሽንግቶን ኤምባሲ ሲለቁ ቆንስላነቱንና አምባሳደርነቱን ደርበው ሰርተዋል። አቶ ፍጹም በኦፊሳል የሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው ሲሾሙ እሳቸው ምክትል አምባሳደር ሆነው በቋሚነት ተመደቡ።

\Related stories   ዓለም ባንክ ተከተለ – ግብጽ ሚስጥሩን ይፋ አደረገች

በሌላ ቋንቋ አቶ ኪዳነ ማርያም የኤምዳሲው አንደኛ ጸሃፊና የፖለቲካ ጉዳዮችን የሚከታተሉ ባለስልጣን ነበሩ። የኢትዮ 12 የቅርብ መረጃ እንዳሉት በትህነግና በመንግስት መካከል ያለውን የዲፕሎማሲ ውዝግብ መንግስት ሆነው በዋናነት የሚከታተሉት እሳቸው ነበሩ። በትህነግ

  • “ደብረ ኤሊያስ ገዳም የደረሰበት ጉዳት የለም” ወረዳው፤ መከላከያ ስራውን መጨረሱ ተሰማ
    አካባባዊ በተለይም ገዳሙ ወታደራዊ ማስለጠኛ፣ የሚፈለጉ ሰዎች መመሸጊያ፣ ሃይማኖታዊ ዓላማውን የሳተ በመሆኑ በአባቶች፣ በሃይማኖት መሪዎች፣ በመንግስት ሃላፊዎችና ታውቃ ሰዎች ቢለመኑም ፈቃደኛ እንዳልሆኑ፣ በስተመጨረሻም ደብሩም ሆነ መኖኮሳቶች ምንም ሳይሆኑ መከላከያ ገብቶ ስራውን አከናውኖ መጨረሱ ተሰማ። በርካታ ታጣቂዎች ለመከላከያ እጃቸውን መስጠታቸውም ተገልጿል። ወረዳው መከላከያ ስራውን ጉዳት ሳያደርስ ማከናወኑን ይፋ ሲያደርግ እጅቻውን ስለሰጡናContinue Reading
  • አሮጌውን ወይን በአዲስ አቁማዳ ! የኖርንበት ፣ የቸከ የሰለቸ የፖለቲካ …
    የኢትዮጵያ ታሪክ የእርስ በእርስ ጦርነት civil war & strife ነው። ይሄንን ያደፈ ጉድለታችንን ማስተካከል የምንችለው መሀከለኛውን መንገድ የያዙ ስብስቦችን በማብዛት ነው። ችግሩ በእኛ ሀገር ፖለቲካ መሀከሉን መንገድ ልትይዝ ስትሞክር የሚወረወርብህ ፍላጻ መብዛቱ ነው። ለዚህ ጥሩ ምሳሌ ኢዜማ ነው። ህወሃትም ፣ የኦሮሞ ብሄረተኜችም ፣ በቅርብ የተፈለፈሉት የአማራ ብሄረተኞችም ለፓርቲው ያላቸውን ጥላቻContinue Reading
  • US Special Envoy for HoA Amb Mike Hammer to Visit Ethiopia
     US Special Envoy for the Horn of Africa Ambassador Mike Hammer will visit Ethiopia on May 31 – June 6. In Ethiopia, Ambassador Hammer will meet African Union officials on implementation of the November 2, 2022 Cessation of Hostilities Agreement (COHA). He will discuss progress and priorities including transitional justiceContinue Reading
  • በሽብር ወንጀል በተጠረጠሩ በ38 ግለሰቦች ላይ ተጨማሪ የ14 ቀን ጊዜ ተፈቀደ
    የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት በ3 መዝገብ የቀረቡ የ38 ተጠርጣሪዎችን ጉዳይ ተመልክቷል። ተጠርጣሪዎቹን ፍርድ ቤት ያቀረበው የፌደራል ፖሊስ መርማሪ በቀዳሚነት በነመላክ ምሳሌ መንግስቱ መዝገብ የተካተቱ 16 ግለሰቦችን እና በነደበበ በሻህ ውረድ መዝገብ የተካተቱ በ12 ተጠርጣሪዎች አጠቃላይ 26 ግለሰቦች ላይ የሽብር ወንጀል የጥርጣሬ መነሻውን በፅሁፍም በቃልምContinue Reading
  • ሟችን በጭፈራ የሚሸኘው ማህበረሰን
    በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በኮንሶ ዞን ውስጥ ተወልደው ያደጉት ዶ/ር ኦንጋዬ ኦዳታ በቅርቡ ነው አያታቸውን በሞት ያጡት። የሚወዷቸው አያታቸው ቀብር የተፈፀመው ግን ወዳጅ ዘመድ ተሰብስቦ ዘፍኖ እና ጨፍሮ በተከናወነ ሥነ ሥርዓነት መሆኑን ከቢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል። ሞት በሁሉም ዘንድ ሁሌም አዲስ ነው። በመጣ ቁጥር የሚያስደነግጥ በብዙ ማኅበረሰቦች ዘንድም ማቅ የሚያስለብስContinue Reading

Leave a Reply