የአሜሪካ መንግስት የ550 ሚሊዮን ዶላር በጀት ማጽደቁን የአሜሪካ የአለም አቀፍ ልማት ኤጀንሲ ዩ.ኤስ. አይ.ዲ የኢትዮጵያ ሚሽን ዳይሬክተር የሆኑት ሚስተር ሲን ጆንስ አስታወቁ። በራሳቸው፣ በአሜሪካ ህዝብና መንግሥትን ስም አገራቸው የምትከተለውን አቋም ይፋ ማድረጋቸውን አመልክተዋል። ዜናው ኢትዮጵያ ላይ የነበረው ጫና እየተላዘበ ለመምጣቱ አመላካች እንደሆነ ተመልክቷል።
ዳይሬክተሩ በመግለጫቸው እንዳስታወቁት የአሜሪካ መንግስት ከኢትዮጵያ ጋር እጅ ለእጅ ተያይዞ ስራዎቹን እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። ከኢትዮጵያ መንግስታና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እጅ ለጅ በመያያዘ እንደሚሰሩ ሲናገሩ ዋና ዓላማው የምግብ ምርት ራስን የማስቻል ዓላማን ለምሳካት መሆኑንን አመለክተዋል።
በአሜሪካ ህዝብ እና መንግስት የሚታገዘው ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም (PSNP) ለመጭዎቹ አምስት አመታት በኢትዮጵያ ተጠናክሮ ይቀጥላል እንደሚቀጥል የተናገሩት አስረግተው ነው። ለዚህ ፕሮግራምም የአሜሪካ መንግስት 550 ሚሊየን ዶላር እንደመደበም ይፋ አድረገዋል።
ፕሮጀክቱ ዘጠኝ ሚሊየን ኢትዮጵያውያንን ተጠቃሚ የሚያደርግ እንደሆነ አመልክተዋል። ሃላፊው ሁሉን ካሉ በሁዋላ የኢትዮጵያን መንግስት ላለው የአመራር ቁርጠኛነት (commitment and leadership) የአሜሪካ መንግስት አድናቆት እንዳለው ሳይሸሽጉ ገልጸዋል። የሁለቱ አገራት ግንኙነት የበለጠ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አጽንዖት ሰጥተው አስታውቀዋል።
ዜናው ኢትዮጵያ ላይ ተከፍቶ የነበረው ዘመቻ መላዘቡን የሚያሳይ እንደሆነ ተመልክቷል። ከዚህም በተጨማሪ በኢትዮጵያና አሜሪካ መካከል ተፈጥሮ የነበረው ልዩነት ወደ ነበረበት እየተመለሰ ለመሆኑ አመካች እንደሆነም የጠቆሙ አሉ።
ከአምስት አመት በፊት በእንጀራ እናቷ ተገደለች የተባለችው ግለሰብ በህይወት ተገኘች by topzena1
April 18, 2021 በሰሜን ሸዋ ዞን ሞጃና ወደራ ወረዳ ከአምስት ዓመት በፊት በእንጀራ እናቷ ተገደለች የተባለችው ግለሰብ በህይወት መገኘቷ ታወቀ። ግለሰቧ መሞቷ በሀሰተኛ ምስክሮች ተረጋግጦ የእንጀራ እናቷ የ20 ዓመት እስር ቅጣት ተጥሎባቸው ነበር። ሞታለች የተባለችው ግለሰብ እና ከሳሽ የነበሩት በቁጥጥር ስር ውለዋል። የዞኑ ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ህዝብ ግንኙነት ባለሙያ ኮማንደር ደበበ […]
“ሌሎች ህወሃቶችና ኦነግ ሸኔ ጨረሱን” የአጣዬ ነዋሪዎች ” ጅብ የሚነክሰው አናክሶ ነው ” የአቶ ምግባሩ ትንቢት by topzena1
April 18, 2021 በክፉዎች ሴራ ቤተሰቦቻቸው፣ የአማራ ክልል፣ ኢትዮጵያና ወዳጆቻቸው ያጡዋቸው አቶ ምግባሩ ከበደና ባልደረቦቻቸው የሚረሱ እንዳልሆኑ በሁሉም ዘንድ እምነት አለ። ዶ/ር አምባቸው መኮንን፣ የክልሉ ጠቅላይ አቃቤ ሕግ የአቶ ምግባሩ ከበደና የርዕሰ መስተዳደሩ አማካሪ የአቶ እዘዝ ዋሴ በጁን 25 ቀን 2019 የቀብር ስነስርዓታቸው የተከናወነው በክፉዎች ሴራ መሆኑንን መላው የአማራ ሕዝብ ጠንቅቆ […]
የአማራ ሕዝብ ከፖለቲካ ነጋዴዎች ራሱን አግልሎ በአንድነት ይቁም!! ሰሜን ሸዋ፣ ጭልጋ፣ ፍኖተ ሰላም አማራ እየተወጋ ነው by topzena1
April 17, 2021 የክልሉ የሰላምና ሕዝብ ደኀንነት ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ ሲሳይ ዳምጤ ሲናገሩ እንደተሰማው በሰሜን ሸዋ ያለው ሁኔታ የከፋ ነው። አማራ አንድ ሆኖ መነሳት አለበት። የአካባቢውን አመራሮች የጠቀሱ የሌሎች ሚዲያዎች እንዳሉት ወራሪው ሃይል እጅግ ብዙ ነው። አሁን ስፍራው ላይ ያለው ሊቋቋመው አይችልም። አቶ ሲሳይ ” አማራ በአንድ ይቁም” ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል። […]
“ሁሉንም ያማከለ ዴሞክራሲያዊ ስረዓተ መንግስት ካልተመሰረተ ወቅታዊና ረጅም ጊዜ ያስቆጠሩ ችግሮች ለመፍታት አስቸጋሪ ነው” by topzena1
April 17, 2021 በኢትዮጵያ እውነተኛ ሁሉንም ያማከለ ዴሞክራሲያሲዊ ስረዓተ መንግስት ካልተመሰረተ አሁን ያሉትንና ረጅም ጊዜ ያስቆጠሩ የአገሪቱን ችግሮች ለመፍታት ከባድ ሊሆን እንደሚችል በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ምክክር ያደረጉ ምሁራን ገለጹ። ‘ኢትዮጵያዊነት’ በተሰኘ የሲቪክ ማኅበር አዘጋጅነት ምዕራባውያን በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ያያዙትን የተሳሳተ አቋም በተመለከተ በአለም አቀፍ ደረጃ የዌቢናር ውይይት እየተካሄደ ነው። በውይይቱ […]
Like this: Like Loading...
Related