የሰላም ሚንስትር ወ/ሮ ሙፈሪያት ከቅጥር ነብሰ ገዳዮች አመለጡ፤ ” እኔ ውስጥ እናንተ፣እናንተ ውስጥ እኔ አለን”

የሰላም ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል ከትህነግ የቅጥረ ነበሰ ገዳይ ቡድኖች ቀለበት ማምለጣቸው ተሰማ። ግድያው የከሸፈው የአገር ደህንነት ቀድሞ መረጃ አግኝቶ ይሁን አይሁን አልታወቀም። መንግስትም በይፋ አላሳወቀም። ትግራይ በስለም ኮንፍረንስ ላይ ” እኔ ውስጥ እናንተ፣እናንተ ውስጥ እኔ አለን” በሚል እንባ እየተናነቃቸው ያስተላለፉት የሰላም ጥሪ ለሚኒስትሯ እንደ ታላቅ ታሪካዊ ሰነድ ሆኖ የተያዘ ንግግር መሆኑ አይዘነጋም።

ከህግ ማስከበሩ ዘመቻ በሁዋላ በትግራይ የሚላስ የሚቀመስ መጥፋቱ በትግያ ተወላጆች ከፈተኛ ጩኸትና ተቃውሞ የቀረበበት ጉዳይ ነበር። መንግስት ለጉዳይ ልዩ ትኩረት በመስጠት ወ/ሮ ሙፈሪያትን ወደ ትግራይ ልኮ ለሶስት ሳምንት ያህል እዛ ሆነው ከዓለም ዓቀፍ እርዳታ ተቋማት ጋር ሲሰሩ እንደነበር ይታወቃል።

ከዓለም የምግብ ድርጅት ባለስልጣናት፣ ከተለያዩ የዓለም አቀፍ ድርጅቶች፣ የአውሮፓና አሜሪካ ተወካዮች እንዲሁም ከተለያዩ ለጋሽ አገሮች ጋር በመቀሌ ሆነው አብረው ሲሰሩ እነደከረሙ ዜናዎች ሲሰራጩ ነበር። በትክክል ያለውን መረጃ በአካል በመገኘት በማስረዳት ሰፊ ስራ የሰሩትና በርካታ ሪፖርቶች እንዲላዘቡ ሃቅ ያስጨበጡት ወ/ሮ ሙፈሪያት፣ ከህግ ማስከበሩ ዘመቻ በፊት ጀምሮ እያለቀሱ ሰላም እንዲወርድ ሲማጸኑ  ተግባራቸው አልተወደደላቸውም ነበር።

በርካታ የትህነግ ደጋፊዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች ” ኮበለሉ” ከሚለው የሃሰት ዜና ጀመሮ ከፍተኛ ስድብ ሲያወርዱባቸው ነበር የሰነበቱት። አንዳንዶቹ ዛቻም ያሰሙ ነበር።

ወ/ሮ ሙፈሪያት ታስቦበት ይሁን በድንገት ባስቸኳይ ወደ አዲስ አበባ እንዲመጡ ጥሪ የደረሳቸው በቀጥታ ለሳቸው እንደነበር የዛጎል መረጃ አቀባይ አስታውቀዋል። መረጃው በደረሳቸው ቅጽበት በመከላከያ ሰራዊት እይታ ውስጥ ሆነው አውሮፕላን ተሳፈሩ።

እሳቸው ወደ አዲስ አበባ ካመሩ በሁዋላ በትግራይ ለእሳቸው በተመደበቸው ተሽከረካሪ ላይ ጥቃት ተሰነዘረ። መረጃውን ያጋሩት እንዳሉት ሁለት ሰዎች ተጎድተዋል። ማንነታቸውን ግን ለጊዜው ማወቅ አልቻሉም።

” መተናኮስ አገርን ከመከፋፈል የተለየ አይደለም” ሲሉ መቀለ በሰላም ኮንፈራንስ ላይ ንግግር አድረገው ነበር። በዛው ንግግራቸው እብሪት፣ንቀት፣ እኔ ከሌላው እበልጣለሁ ማለት እንዴት እንደመጣ፤ በለው፣ ፈለጠው፣ ቁረጠው … የሚለው ፉከራ እንዴት ሊመታ ቻለ በሚል እያለቀሱ ሰላምን ሲማጸኑ እንደነበር ይታወቃል።

See also  ከመወሰንህ በፊት ረገብ በል !

መረጃ ካቀበሉን ውጪ ዜናውን የመንግስትም ሆነ የትግራይ ክልል አላረጋገጡም። ትግራይ ክልል የሚኖር የማህበራዊ ገጽ ተባባሪያችን ለማጣራት አንድ ሃላፊ ጋር ደውሎ ለማናገር ቢሞክርም ሃላው ምንም ለማለት ፈቃደኛ እንዳልሆኑ ገልጸው ስልካቸውን ዘግተዋል። ይሁን እንጂ ጥያቄውን ስምተው አላስተባበሉም።


  • የተጠልፈቸው ጸጋ በላቸው ነጻ ሆነች፤ ጠላፊው አልተያዘም
    ወይዘሪት ፀጋ በላቸውን ከተጠርጣሪው ግለሰብ ማስጣል መቻሉን የሲዳማ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ አስታወቀ። የሲዳማ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሃላፊ አቶ አለማየሁ ጢሞቲዮስ ጉዳዩን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ በተደረገው የተቀናጀ የፀጥታ ኦፕሬሽን በተጠርጣሪው ግለሰብ የተጠለፈችውን ወይዘሪት ፀጋ በላቸውን ማስጣል መቻሉን ተናግረዋል። ግንቦት 15 ቀን 2015 ከመደበኛ ስራዋ ወጥታ ወደቤቷ ስታቀና ተጠርጣሪው ግለሰብContinue Reading
  • ፌደራል ፖሊስ ሆን ብለው ሐሰተኛ መረጃ በሚያሰራጩ አካላት ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል አለ
    ሆን ብለው ሕብረተሰቡን ለማሳሳት ሐሰተኛ መረጃ በሚያሰራጩ ግለሰቦች ላይ እየወሰደ ያለውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታወቀ። ተቋሙ አገራዊ ለውጡን ተከትሎ መንግስት ለህዝብ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ከወሰዳቸው እርምጃዎች መካከል የሰብአዊ መብት ጥሰት ይፈፀምበት የነበረውን ማዕከላዊ የወንጀል ምርመራን መዝጋት መሆኑንና ይሄንን ተከትሎ በፖሊስ የወንጀል ምርመራ ስራ ላይ ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበትContinue Reading
  • ኢሰመኮ ሁለት ሰዎች ሲሞቱ በርካቶች የጸጥታ ሃይሎችን ጨምሮ ጉዳት እንደደረሰባቸው አስታወቀ
    በሸገር ከተማ ከመስጊዶች መፍረስ ጋር ተያይዞ የተነሱ ተቃውሞዎችን እና የደረሰ ጉዳትን በተመለከተ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከግንቦት 18 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ በተለይም በአዲስ አበባ አንዋር መስጊድ ውስጥ እና በተወሰኑ አካባቢዎች በሸገር ከተማ በመንግሥት አካላት ከፈረሱ መስጊዶች ጉዳይ ጋር ተያይዞ የተነሱ ተቃውሞዎችን ተከትሎ የደረሰውን የሰዎች ሞት እና ጉዳቶችን በተመለከተContinue Reading
  • አዲስ አበባና በሸገር ከተሞች የፈረሱትን ቤቶችና ማህበራዊ ቀውስ አስመልክቶ ኢሰመኮ መገለጫ አወጣ
    በአዲስ አበባ እና በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተሞች እየተካሄደ ነው ባለው የቤት ፈረሳ እና የግዳጅ የማስነሳት ሂደት 111 ሺህ 811 ቤቶች መፍረሳቸውን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) አስታወቀ። ኢሰመጉ ይህንን የገለጸው ከጥቅምት 2015 ዓ.ም. ጀምሮ በጉዳዩ ላይ ያካሄደውን የምርመራ ሪፖርት ግንቦት 23/2015 ዓ.ም. ይፋ ባደረገበት ጊዜ ነው። ኮሚሽኑ ይህንን አሃዝ ይፋContinue Reading

Leave a Reply