- በአሸረቅ S24 ቴሌቪዥን ሱዳናዊ ምሁርና ባለስልጣን የሰጡት ሐሳብ ነው።
° ጋዜጠኛው — “ለዚህ አባባልዎ ማስረጃ አለዎት?”
“ብዙ አለ ። ዋናው መሠረታዊ ችግር ከአባይ ወንዝ አጠቅላይ ውሃ 50 ቢሊዮን ኪዩቢክ ምንጩ ብሉናይል ነው ይህ ከፍተኛ ውሃ ሚመጣው ደግሞ ለ3 ወር ነው
ማለትም ከጁን አጋማሽ እስከ ሴብቴምበር ግማሽ
ከዚህ በኋላ የውሀው ሀይል ይዳከማል እናም ለግብርና ለኤሌትሪክ ሀይልም ሆነ ለሌሎች ፍላጎት መጠቀም አይቻልም እናም ሱዳን ከውሃው ሚጠቀመው 3 ወር ብቻ ነው።
“ከህዳሴ ግድቡ ማለቅ በኋላ ግን የአባይ ውሃ ፍሰቱን ሳያቋርጥ አመቱን ሙሉ ተስተካክሎ ይደርሱናል
በዚህም ግብፅ በአስዋን ግድብ ተጠቅማ በአመት 3 ግዜ ከእርሻ ምርት እንደምታገኘው ሁሉ ሱዳንም በአመት አንዴ ብቻ የነበረውን 3 ግዜ ማምረት ትችላለች በአመት አንዴ ብቻ እንድንዘራ ያደረገንም የውሀው ፍሰት ለ 3 ወር ብቻ በመሆኑ ነው የህዳሴው ግድብ ግን አመቱን ሙሉ ውሃ እንድናገኝ ያረጋናል።”
“ይህ ብቻ አደለም እንደ እርሻ ምርቱ ሁሉ የአልመረዊ ግድብም የተስተካከለ ኤሌትሪክ ሀይል ማመንጨት ይችላል
የመራዊ ግድብ ከ Feb — April ሀይል የማመንጨት አቅም ደካማ እና የተቆራረጠ ነው ። ከግድቡ የሚለቀቀውን ውሃ ተርባይኖችን ማዞር ስለሚችል የሀይል ማመንጨት አቅሙ የተስተካከለ ይሆናል”

~ ከ 1959 ስምምነታችን ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ ሱዳን ካላት ከውሃ ዴርሻ 6.5 ቢሊዮን ኪዩቢክ ውሃ መጠቀም አለመቻሏን የቀድሞ ውሀና መስኖ ሚ/ር ከማል አሊ ገልፀዋል ። ከዚህ ሌላ ተጨማሪ 3.5 ቢሊየን ውሃ ከክረምቱ ዝናብ ሃያልነት ከሚገኝ በአጠቃላይ 10 ቢሊየን ኪዩቢክ ውሃ በእየአመቱ ታጣለች። ሱዳን ይህን ለመጠቀም ሞክራ ያልተሳካለት ውሃ በቀጥታ ወደ አስዋን ግድብ ነው ሚገባው።
“የህዳሴው ግድብ ይህን 10 ቢሊዮን ኪዩቢክ ውሃ ወደ ግብፅ እንዳይፈስ ስለሚከላከልልን ቅድም ያልኩህን በአመት 3 ግዜ ማምረት እንድንችል እና የኤሌትሪክ ሀይልም በተስተካከለ መልክ እንድናገኝ ያደርጋል”
ጋዜጠኛው በመሀል “መርሳት የሌለብህ እሚሉት እና ሚፈልጉት ከ1959 ሳይሆን ከአሁን ወቅታዊ ወቅታዊ ሁኔታ እንጀምር ነው” ?
“የህዳሴው ግድብ የሱዳንን ውሀ ድርሻ ስለሚያስከብርልን ይህ 10 ቢሊየን ውሃ ወደ ግብፅ መሔድ አይችልም ። ስለዚህ የግብፅ ፍትጊያ ግራ ማጋባት እና ጩኸት መሠረታዊ ምክንያት ይህ የሱዳን ድርሻ የሚያጡት 10 ቢሊዮን ውሃ ነው ስለዚህም ዋናው ችግር ያለው ከሱዳን እንጅ ከኢትዮጵያ ጋር አደለም።
ይህ የሱዳን ጥቅም መጥጠበቅ ሲገለጥላቸው ለምን በሚል አየፈጠረ ያለ ችግር ነው ችግራቸው ሱዳን ለምን ትጠቀማለች ነው”
ጋዜጠኛው “ከውሀ ሚ/ር ሀላፊዎች አሁንም የሱዳንን ከዚህ ግድብ ተጠቃሚነት ሲናገሩ ሱዳን ከኢትዮጵያ በበለጠ ተጠቃሚ እንደሆነች ነው ሚናገሩት” ?
“በሚገባ! ይህን ዶ.ር ማህመድ አቡዘይድ ዶ.ር ሶፍወት አብድ አድዳኢም እና ልሎችም ሀላፊዎች በሚገባ ተናግረዋል።ሌላውን የደለል ጉዳይ ነው። ባለፉት አመታት የኤሌክትሪክ መቆራረጥ ችግሮች መንስኤው በከፍተኛ ደለል ክምችት ተርባይኖች ስራ ማቆም መሆኑን ኦፊሴላዊ መግለጫ በባለስልጣኑ መግለጫ ሲነገረን ኑሯል
የህዳሴው ግድብ ይህን የደለል ክምችት በከፍተኛ ደረጃ ይከላከላል ያስቆምልናል። በዚህም የሮዛሬስ እና አልመረዊ ግድቦች ሌሎችም ያለ ችግር ስራቸውን ይሰራሉ።
“የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ዋጋ ከሱዳን አኳያ በጣም ቅናሽ ይኖረዋል እናም ሱዳን እንደ ካጅባር ፣ ሽሬክ ፣ ዳልል እና የመሳሰሉ ግድቦችን መገንባት ሳያስፈልጋት ከኢትዮ ሱዳን የተጀመረውን የኤሌትሪክ ሀይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታ አጠንክሮ ሰርቶ በመጨረስ የሀይል ፍላጎታችንን በቅናሽ ዋጋ ከኢትዮጵያ መግዛት ይቻለናል”
“የውሀ ክምችት፣ግብፅ 162 ቢሊዮን ኪዩቢክ ውሀ ክምችት የመያዝ አቅም ነው ያላት። ባንፃሩ ሱዳን ደግሞ የማከማቸት አቅሟ 10 ቢሊዮን ነው (ይህን አቶ ሰኢድም ሊያረጋግጥልህ ይችላል)። በመሆኑም የሱዳን መንግስት ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ተነጋግረው የሱዳንን ውሃ ድርሻ በህዳሴው ግድብ ሀይቅ በማቆየት በብሉ ናይል ግዛት ለመስኖ እርሻ መጠቀም ይቻለናል ።
ወንድም ጧሒር! (አወያዩን) ከህዳሴው ግድብ ሱዳን ምታገኘው ጥቅም ከዚህ ሁሉ ከነገርኩህ በጣም በጣም የበዛ ነው ። ይህ በአለም አቀፍ ህግ የተፋሰሱ ታችኛው ሀገሮች ጥቅም በሚል የተገለፀ ነው ።
አንድ ሀገር የዚህ አይነት ትልቅ ግድብ ሲገነባ የጋራ ተጠቃሚ የሆኑ ሀገሮችን ለግንባታው እንዲያዋጡ ያስገድዳል። በካናዳ እና አሜሪካ እንደሆነው ካናዳ ግንባታውን ስታስብ ወደ USA በመሔድ ግድቡ ሚያስገኘውን የጋራ ጥቅም (ልክ እንደ ህዳሴው ግድብ ) በመግለፅ ለግንባታው የተወሰነውን አስከፍላለች ።
እኛ ምንም አልከፈልንም በዜሮ ነው የጥቅሙ ተጋሪ የሆንነው።
“ገራሚ እና አስደናቂው ነገር ግድቡ ይፈርሳል የሚለው የግብፅ ስጋት ንግግር (ባዶ ወሬ ) ነው። እውነት አሁን የግድቡ ደህንነት ስጋት ግብፅን ከሱዳን በበለጠ አስግቷት ነው ? ይገርማል እኮ! በዓለም ዙርያ ከ 45 በላይ ትልልቅ ግድቦች አሉ ። ባለፉት 20_30 አመታት ውስጥ አንድም መፍረሱን አልሰማንም። “የአስዋን ግድብ አይፈርስም የህዳሴ ግድብ ግን ይፈርሳል” አስቂኝ ተረት ።
መታወቅ ያለበት ነገር የአስዋን ግድብ የተገነባው 60ዎቹ ውስጥ በወቅቱ ኋላ ቀር ቴክኖሎጂ በሩሲያን ነው
የህዳሴው ግድብ እየተገገነባ ያለው ደግሞ በ21ኛ ክፍለ ዘመን በወቅቱን የአውሮፓ የቴክኖሎጂ ነው ።
አስዋን ግድብ ውሃ መያዝ አቅም 162 ቢሊዮን
የህዳሴው ግድብ ደግሞ በግማሽ አንሶ 74 ቢሊዮን
እንዴት ነው ሚገናኙት ? ግብፆች ግድቡ ያረፈበት ቦታ የመሬት መንቀጥቀጥ ስጋት አለበት ይሉናል።ኢትዮጵያ ይህ አይነት ችግር የለበትም ማንኛውንም መፅሐፍ ብትገልጥ ወይም የትኛውም ድረ ገፅ ገብተህ ግብፆች ለሚሉት ሁሉ ማረጋገጫ አታገኝም የላቸውምም”
Mahmud Nuru ነው የትርጉሙ ባለቤት 🙏
የዓባይ ልጅ
- በአሜሪካ ብልጽግናን ተክቶ አራት ኪሎ እንዲገባ ” ዳግማዊ ኢህአዴግ” እንደገና እየተበጀ ነው፤ መንግስት ሙሉ መረጃው አለውበአሜሪካና በተለያዩ አገራት የሚገኙ ስደተኛ ፖለቲከኞች ብልጽግናን በመተካት አራት ኪሎ ለመግባት አሜሪካንን እያባበሉ መሆኑ ተሰማ። እንደ ዜናው ከሆነ አቶ ለማ መገርሳ፣ አቶ ገዱ አንዳርጋቸውና የትህነግ የአሜሪካ ህዋስ አሉበት። ስብስቡ ” ዳግማዊ ኢህአዴግ” የሚል ስም በአንዳንድ ተጋባዦች እየተሰተው ነው። ለውጡን በሙሉ አቅሟ ደግፋ የነበረችው አሜሪካ በቅጽበት የብልጽግናን መንግስትና መሪውን ዶክተር አብይ … Read moreContinue Reading
- ኢዜማ እስር ላይ ያሉት መሪው ዶክተር ጫኔ የድርጅቱን መርህ መጣሳቸውን በይፋ አስታወቀኢዜማ እስር ላይ ያሉት የድርጅቱ መሪ ዶክተር ጫኔ ከበደ የድርጅቱን መርህ መጣሳቸውን በይፋ አስታወቀ። ድርጅቱ ባወጣው መግለጫ ከድርጅቱ መርህ ውጭ ባፈነገጠ መልኩ መንቀሳቀስ ኢዜማን እንደማፍረስ እንደሚቆጠር አስታውቋል። የድርጅቱን መርህና አሰራር የዘርዘረው መግለጫ ” የፓርቲያችን ሊቀመንበር ጉዳይም ከዚህ ከላይ ከተገለፀው መርኅ አንጻር የሚታይ ይሆናል ሲል ፓርቲያችን ይገልፃል” ሲል አቋሙን ይፋ አድርጓል። … Read moreContinue Reading
- የመከላከያን ጨምሮ የአሜሪካንን ሚስጢር “ለትውልድ አገሩ አቀብሏል” የተባለው ትውልደ ኢትዮጵያዊ ” ብሄራዊ ጀግና” እየተባለ ነውባለፉት ሁለት የጦርነት ዓመታት ኢትዮጵያ ላይ የሚያሴሩ፣ ራሳቸውን ሸጠው ኢትዮጵያን የሚያደሙና የቀጠራቸውን አገር ፍላጎት ለማሳካት ውል ገብተው በጋዜጠኛነት ስም ፕሮፓጋንዳ የሚያሰራጩ “ልጆቿን” በገሃድ አይታለች። ዓለም “ታላላቅ” በሚባሉ መሪዎችና ዓለም ዓቀፍ ተቋማት፣ ሚዲያዎች፣ አገራትና ህብረት ስም ኢትዮጵያን ለማወላለቅ ተባብሮ ሲዘምት እነዚሁ ወገኖች አብረው ተሰልፈው ሲያሸረግዱና ለገቡት ውል አፈንድደው የኢትዮጵያን ውድቀት ሲያሳልጡ … Read moreContinue Reading
- በአማራ ክልል ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል፤ “በተፈጠረው የሰላም እጦት ክልሉ ከፍተኛ ገቢ እያጣ ነው”“በተፈጠረው የሰላም እጦት ክልሉ ከፍተኛ ገቢ እያጣ ነው” ሲል የክልሉ ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ አስታወቀ። በክልሉ እየታየ ያለው የሰላም እጦት በኢንቨስትመንቱ ላይ ቀጥተኛ የኾነ ተጽእኖ እያሳደረ እንደኾነ ነው የአማራ ክልል ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ የገለጸው፡፡ እየታየ ያለው አለመረጋጋት ወደ ክልሉ እየገባ ያለውን እና ለመግባት በሂደት ላይ የነበረውን ኢንቨስትመንት እንደሚያስቀር ተገልጿል። … Read moreContinue Reading
- የባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ ለኢንቨስተሮች መሰጠቱን የተቃወሙ ሦስት ምሁራን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ደብዳቤ ጻፉ“እሳቸው ይሄንን ነገር ሰምተውታል ብዬ አላስብም። ከሰሙ እንደሚያስቆሙት እርግጠኛ ነኝ” ከአምስት አስርት ዓመታት በላይ ያስቆጠረው የባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ ከፊል ስፍራ ተቆርሶ ለግብርና ኢንቨስተሮች መሰጠቱ ያስቆጣቸው ሦስት ምሁራን ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ደብዳቤ ጻፉ። የባቢሌ ፓርክ ደን ተመንጥሮ ለኢንቨስተሮች መሰጠቱ ከፍተኛ የድርቅ አደጋ እንደሚጋርጥ በመግለጽም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጣልቃ እንዲገቡ ምሁራኑ በደብዳቤያቸው … Read moreContinue Reading
- የበርሊን ማራቶን ባለማዕረግ ትግስት እነ ዱቤ ጂሎ ቢሳተፉ ታዝረከርካቸው ነበርበማራቶን ከሁለት ደቂቃ በላይ ማሻሻል እጅግ የሚደነቅና ያልተለመደ ነው። ባለሙያዎቹ ወይም አሰልጣኞቹ የሮጠችበትን ፍጥነት በሰዓትና ርቀት ከፋፍለው ቢያቀርቡት ምን አልባትም ወንዶችን የሚገዳደር ፍጥነት ተጠቅማ ሮጣለች። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ተቴክኒክ ዳይሬክተርና የአትሌቶች ኮሚሽን ሰብሳቢ የነበሩት የዛሬው የተከበሩ ዱቤ ጅሎ አይነቱን ሯጮችን አዝረክርኮ ማሸነፍ የሚያስችላትን ሃይል አሳይታለች። የበርሊና ባለ ማዕረግ ትዕግስት!! ተግስት … Read moreContinue Reading