የአገር መከላከያ ሰራዊት ” ርዝራዥ” ሲል የሚጠራውን ሃይል መደምሰሱን አስታወቀ። ሃይሉ የተደመሰሰው ድንበር አቋርጦ ወደ ሱዳን ለመሸሽ በሞከረበት ወቅት እንደሆነ ታውቋል። ከተገደሉት በፍተሻ ” የኦሮሞ ማንነት መታወቂያ ተሰርቶላቸው ነበር” ተብሏል።
የኢፌዲሪ መከላከያ ሰራዊት የግንባታ ስራዎች ዋና አስተባባሪ ሌ/ጄነራል ባጫ ደበሌ እንደገለጹት የጁንታው አባላት በከፍተኛ ዝግጅት ነበር ከአገር ለመውጣት ሙከራ ያደረጉት። ቀደም ባለው መግለጫቸው በዚሁ ሃይል ላይ በስምንት አቅጣጫዎች በተወሰደ እርምጃ የተርፈው ሃይል ተበታትኖ ከአገር እንዳይወጣ ስራ መሰራቱን አስታወቀው እንደነበር ይታወሳል።
ሌ/ጄነራል ባጫ ደበሌ ዛሬ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሲሰጡ ፣ ርዝራዡ የጁንታው አባላት ወደ ሱዳን ሲሄዱ በቀላሉ ማለፍ እንዲችሉ ያዘጋጁት የኦሮሞ ማንነት እንዳላቸው የሚያስመስል መታወቂያ ነው። ከዚህም በተጨማሪ አለባበሳቸውን ቀይረው ነበር። ይሁን እንጂ አስቀድሞ በተዘረጋ ስልትና እቅድ መሰረት ሃሳቡ ሳያሳካ ቀርቷል። መከላከያ በክትትል ደርሶ እርምጃ ወስዷል። አብዛኞቹ ሲደመሰሱ የተቀሩት ወደ ጉድጓድ መጋታቸው ተገልጿል።
ወደ ሱዳን ለመግባት የተፈለገበት ዋና ምክንያት ሱዳን ተቀምጠው አገር ውስጥ ያሉትን ታጣቂ ሀይሎች በሽምቅ ውጊያ በማሰማራት ሀገር ለመበጥበጥ ባለው ዕቅድ መነሻ እንደነበር ሌ/ጄነራል ባጫ በመግለጫቸው አስረድተዋል። እርምጃ በተወሰደባቸው ሁሉም የጁንታው አባላት እጅ ላይ የሀሰተኛ መታወቂያ እንድተገኘባቸው አመልክተዋል።
- ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በከፍተኛ የውስጥ ችግር ውስጥ ናት፤ በጾሙ ማቅ ለብሰው በንስሃ ችግራቸውን ይፍቱየኢትዮጵያ ታሪክ ቁንጮ እንደሆነች የሚመሰከርላትና እጅግ ውብ ስብዕና ያላቸው አባቶች… Read more: ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በከፍተኛ የውስጥ ችግር ውስጥ ናት፤ በጾሙ ማቅ ለብሰው በንስሃ ችግራቸውን ይፍቱ
- ሕብረቱ ከታገዱ የሩሲያ ንብረቶች የሚገኘውን ትርፍ ለዩክሬን ጦር መሳሪያ ግዢ ሊያውል ነውየአውሮፓ ሕብረት በአባል ሀገራቱ እንዳይንቀሳቀሱ ከታገዱ የሩሲያ ንብረቶች የሚገኘውን ትርፍ… Read more: ሕብረቱ ከታገዱ የሩሲያ ንብረቶች የሚገኘውን ትርፍ ለዩክሬን ጦር መሳሪያ ግዢ ሊያውል ነው
- ሳኡዲ የምታስገነባው አዲስ ከተማ – “ኒዮም ሲቲ” (Neom City)በረሃን ወደ ከተማነት የመቀየር ጥበብ ልንለው እንችላለን፡፡ ከ1 ትሪሊየን ዶላር… Read more: ሳኡዲ የምታስገነባው አዲስ ከተማ – “ኒዮም ሲቲ” (Neom City)
- Ethiopia, Somalia dispute won’t transform into turmoil for the Horn of Africadeal between Ethiopia and Somaliland has sent waves of debates… Read more: Ethiopia, Somalia dispute won’t transform into turmoil for the Horn of Africa