“ቤኒሻንጉል ወደ ሱዳን ለመቀላቀል የሚያደርጉትን ትግል አረቦች ይደግፉ”የሚል ጥሪ ቀረበ

ግብጻዊያን የፓለቲካ ተንታኞች እና አክቲቪስቶች ኢትዮጵያን ለማደከምና ለማፍረስ ከአሁን የተሻለ ጊዜ የለም በሚል የተቀናጀ ሥራ እየሰሩ መሆናቸውንና የአረብ አገሮች እገዛ እንዲያደርጉ በግልጽ ጥሪ እያቀረቡ ነው። አምስት ሚሊዮን የሚሆነው የቤኒሻንጉል ሕዝብ ሱዳናዊና አረብ ነው ብለዋል። ይህ የተባለው የአማራ ክልል ላይ የታየውን ተቃውሞ ተከትሎ ነው።

ከሰሞኑ ግብጻዊያኑ የፓለቱካ ተንታኝና አክቲቪስቶች በግልጽ በአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን እና ማህበራዊ ሚዲያዎች ብቅ እያሉ በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ በመግባት የተለያዩ አገር አፍራሽ ሥራዎችን ሃሳብቸውንና ፍላጎታቸውን እየገለጹ ናቸው።

በአገሪቱ ታዋቂ የሆነው የፓለቲካ ተንታኝ ከሰሞኑ በቴሌቪዥን ሥርጭት ላይ ቀርቦ “የቤንሻንጉል ክልል የሡዳን መሬት ሥለሆነ ወደሡዳን ለማካለል የአረብ አገራት ድጋፍ እንዲያደርጉ” ሲል ጥሪ አቅርቧል።

“ቤንሻንጉሎችን መሬቱ የኛ ስለሆነ ለቃችሁ ውጡ እያሉ የአማራ እና የኦሮሞ ብሄር ተወላጆችን እያባረሩዋቸው ነው” ሲል የተናገረው ይህ ግብጻዊ፤ “ግድቡ ያለው በዚሁ ክልል ስለሆነ ጉሙዞች እንደ ደቡብ ሱዳን ህዝቦች ነፃ እንዲወጡ ማገዝ አለብን” ብሏል።

“ይሄንን አጋጣሚ በመጠቀም የአብይ አህመድን መንግስት ማዳከም አለብን ይህንን ማድረግ ካልቻልን ሌላ ተጨማሪ እንድሎችን አናገኝም” በማለት ሲናገር ተደምጧል። በተመሳሳይ ሼሪፍ ኤልሳሊይ የተባለ አክቲቪስት ከሰሞኑ “በኢትዮጵያ በሁሉም ክልሎች ያሉ የሽምቅ ተዋጊዎች’ የግብፅ መንግስት ድጋፍ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፤ መንግስታችንም ይሄንን ተቀብሎ ወደስራ ገብቷል” ሲል መግለጹ ይታወሳል። ይሄው ግለሰብ “የኢትዮጵያ ማዕከላዊ መንግስት ተዳክሟል፤ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር የሚዋጉ ሀይሎች የግብፅ ስትራቴጂካዊ ወዳጆች ናቸው፤ መንግስት መሰራት ያለበትን እየሰራ ነው። ሁሉንም ነገር ለእናተ ማሳወቅ የለበትም” ሲል መግለጹም አይዘነጋም። የግብጻዊውን የፓለቲካ ተንታኝ መልዕክት የያዘውን ቪዲዮ ከስር ያለውን ሊንክ ተጭነው ያገኙታል ሲል የዘገበው ኢፕድ ነው።


  • የተጠልፈቸው ጸጋ በላቸው ነጻ ሆነች፤ ጠላፊው አልተያዘም
    ወይዘሪት ፀጋ በላቸውን ከተጠርጣሪው ግለሰብ ማስጣል መቻሉን የሲዳማ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ አስታወቀ። የሲዳማ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሃላፊ አቶ አለማየሁ ጢሞቲዮስ ጉዳዩን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ በተደረገው የተቀናጀ የፀጥታ ኦፕሬሽን በተጠርጣሪው ግለሰብ የተጠለፈችውን ወይዘሪት ፀጋ በላቸውን ማስጣል መቻሉን ተናግረዋል። ግንቦት 15 ቀን 2015 ከመደበኛ ስራዋ ወጥታ ወደቤቷ ስታቀና ተጠርጣሪው ግለሰብContinue Reading
  • ፌደራል ፖሊስ ሆን ብለው ሐሰተኛ መረጃ በሚያሰራጩ አካላት ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል አለ
    ሆን ብለው ሕብረተሰቡን ለማሳሳት ሐሰተኛ መረጃ በሚያሰራጩ ግለሰቦች ላይ እየወሰደ ያለውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታወቀ። ተቋሙ አገራዊ ለውጡን ተከትሎ መንግስት ለህዝብ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ከወሰዳቸው እርምጃዎች መካከል የሰብአዊ መብት ጥሰት ይፈፀምበት የነበረውን ማዕከላዊ የወንጀል ምርመራን መዝጋት መሆኑንና ይሄንን ተከትሎ በፖሊስ የወንጀል ምርመራ ስራ ላይ ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበትContinue Reading
  • ኢሰመኮ ሁለት ሰዎች ሲሞቱ በርካቶች የጸጥታ ሃይሎችን ጨምሮ ጉዳት እንደደረሰባቸው አስታወቀ
    በሸገር ከተማ ከመስጊዶች መፍረስ ጋር ተያይዞ የተነሱ ተቃውሞዎችን እና የደረሰ ጉዳትን በተመለከተ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከግንቦት 18 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ በተለይም በአዲስ አበባ አንዋር መስጊድ ውስጥ እና በተወሰኑ አካባቢዎች በሸገር ከተማ በመንግሥት አካላት ከፈረሱ መስጊዶች ጉዳይ ጋር ተያይዞ የተነሱ ተቃውሞዎችን ተከትሎ የደረሰውን የሰዎች ሞት እና ጉዳቶችን በተመለከተContinue Reading
  • አዲስ አበባና በሸገር ከተሞች የፈረሱትን ቤቶችና ማህበራዊ ቀውስ አስመልክቶ ኢሰመኮ መገለጫ አወጣ
    በአዲስ አበባ እና በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተሞች እየተካሄደ ነው ባለው የቤት ፈረሳ እና የግዳጅ የማስነሳት ሂደት 111 ሺህ 811 ቤቶች መፍረሳቸውን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) አስታወቀ። ኢሰመጉ ይህንን የገለጸው ከጥቅምት 2015 ዓ.ም. ጀምሮ በጉዳዩ ላይ ያካሄደውን የምርመራ ሪፖርት ግንቦት 23/2015 ዓ.ም. ይፋ ባደረገበት ጊዜ ነው። ኮሚሽኑ ይህንን አሃዝ ይፋContinue Reading
See also  “ብሔራዊ መግባባት እንዲኖር በትኩረት እሰራለሁ ”አብን

Leave a Reply