የቴሌግራፍ ዘጋቢ ዊል ብራውን በትግራይ ክልል የተካሄደውን የህግ ማስከበር ዘመቻን ተከትሎ ባወጣው ዘገባ “መንግስት በትግራይ ክልል የኬሚካል ጦር መሳሪያ ተጠቅሟል” ሲል ላወጣው ዘገባ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባጭሩ “በአሁኑ ወቅት በአገሪቷ ላይ ጫና ለማሳደር ከሚደረገው ጥረት ተለይቶ ሊታይ አይችልም” ሲል ነው መረጃ ያሰራጨው።
ሁሉም ተብሎ ካለቀ በሁዋላ የተፈለገው ባለመሳካቱ አቡነ ማቲያስ በሃይማኖት አባትነት በሚመሩት ህዝብ ላይ ዓለም ክንዱን እንዲያነሳ ሲጠይቁ “ጂኖሳይድ ተፈጽሟል” በሚል ነበር። ጫናውን ለማጥበቅ ያለመ ነው በተባለው የአባ ማቲያስ ጥሪ ተከትሎ በኢትዮጵያ ስም የዓለምን የጤና ድርጅት የሚመሩት የትህነግ አመራር ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም አደባባይ ወጥተው እጅግ የተቀነባበረ መግለጫ ሰጡ። “ዘግናኝ” ሲሉ በጠሩት የትግራይ ግጭት የሆነውን ለመግለጽ ቃል እንደሚያጥራቸው አስታውቀው እሳቸውም እንደ አባ ማቲያስ ዓለም ኢትዮጵያ ላይ እጁን እንዲያነሳ ጠይቀዋል።
ይህ ከሆነ በሁዋላ ነው ቴሌግራፍ “የጦር ወንጀል መፈጸሙን የሚያሳይ መረጃ አገኘሁ” ሲል ኢትዮጵያ የተከለከለ መሳሪያ መጠቀሟን የዘገበው። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይን የጦር ወንጀለኛ አድርጎ ለማቅረብ የትህነግ ደጋፊዎች በተደጋጋሚ መዛት የጀመሩት ገና ትግራይን ሳይለቁ እንደነበር የሚያስታውሱ እንዳሉት ውጥኑ ቀደም ሲል ጀምሮ የተቀነባበረ ስለመሆኑ ማስረጃ ነው ይላሉ።
ኢትዮጵያ ተገዳና ሰአራዊቷ ታርዶባት የገባችበትን ጦርነት መልክ ለማስቀየር በየዕለቱ መልካቸውን እየቀያየሩ የሚወጡ መረጃዎች ሄደው ሄደው የኬሚካል ጦር መሳሪያ ተጠቅመዋል የሚል ድምዳሜ ላይ መደረሱ የውጭ ጉዳይ እንዳለው ጫና ማጥበቂያ መሳሪያ፣ የተለመደ የሃሰት ዘገባ ነው። ዘገባው ቅሳነት ገብረሚካኤል የተባለች የ13 ዓመት ታዳጊ አንዷ በኬሚካል መሳሪያ ጉዳት የደረሰባት እንደሆነች አመልክቷል።
መግለጫው እንደሚከተለው ቀርቧል።
“ኢትዮጵያ የኬሚካል ጦር መሳሪያ መጠቀም የሚከለክለውን ሕግ በማስፈጸም ድርጊቱንም በግንባር ቀደምነት ከሚያወግዙ አገራት አንዷ ናት”-የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርግንቦት 16 ቀን 2013
ኢትዮጵያ የኬሚካል ጦር መሳሪያን መጠቀም የሚከለክለውን ሕግ በማስፈጸምና ድርጊቱንም በግንባር ቀደምነት ከሚያወግዙ አገራት አንዷ መሆኗን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ የቴሌግራፍ ዘጋቢ ዊል ብራውን በትግራይ ክልል የተካሄደውን የህግ ማስከበር ዘመቻን ተከትሎ ባወጣው ዘገባ “መንግስት በትግራይ ክልል የኬሚካል ጦር መሳሪያ ተጠቅሟል” በሚል ላሰራጨው የተሳሳተ ጽሁፍ የመረጃውን ሐሰተኛነትና ሃላፊነት የጎደለው መሆኑን ገልጿል።
በመግለጫውም “ኢትዮጵያ እንዲህ አይነት ከፍተኛ ጉዳት የሚያደርሱ የጦር መሳሪያዎችንና በአለም አቀፍ ደረጃ በስምምነት የተቀመጡ ጸረ ኬሚካል መሳሪያ ድንጋጌዎችን በግንባር ቀደምነት ከሚተገብሩ አገራት አንዷ ነች” ብሏል።
የኬሚካል የጦር መሳሪያዎች ሰለባ የሆነችው ኢትዮጵያ የትኛውም አካል በየትኛውም ቦታ የኬሚካል የጦር መሳሪያዎችን ጥቅም ላይ ማዋል በጽኑ እንደምታወግዝ መግለጫው አመላክቷል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከዚህ አስቀድሞ ለአለም አቀፉ ማኅበረሰብ ይህን የመሰለ ሆን ተብሎ የተሳሳተና ኃላፊነት የጎደላቸው ሪፖርቶችን በተመለከተ ተጨማሪ ውጥረትን ከማባባስ ሌላ ዓላማ እንደሌላቸው ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ማስታወቁን ገልጿል።
አሁን የተሰራጨው ሐሰተኛና ሃላፊነት የጎደለው ዘገባም በአሁኑ ወቅት በአገሪቷ ላይ ጫና ለማሳደር ከሚደረገው ጥረት ተለይቶ ሊታይ አይችልም ብሏል።የኬሚካል የጦር መሳሪያዎችን ማምረት፣ ማከማቸትና ጥቅም ላይ ማዋል የሚከለከለው ስምምነት የተዘጋጀው እ.ኤ.አ በ1993 መቀመጫውን በኔዘርላድ ሄግ ባደረገው የኬሚካል የጦር መሳሪያ ክልከላ ድርጅት አማካኝነት ነው። በዚህም ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች 193 አገራት ስምምነቱን የፈረሙ ሲሆን ስምምነቱ ከእ.አ.አ 1997 ጀምሮ ተግባራዊ እየሆነ ይገኛል።
- የባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ ለኢንቨስተሮች መሰጠቱን የተቃወሙ ሦስት ምሁራን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ደብዳቤ ጻፉ“እሳቸው ይሄንን ነገር ሰምተውታል ብዬ አላስብም። ከሰሙ እንደሚያስቆሙት እርግጠኛ ነኝ” ከአምስት አስርት ዓመታት በላይ ያስቆጠረው የባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ ከፊል ስፍራ ተቆርሶ ለግብርና ኢንቨስተሮች መሰጠቱ ያስቆጣቸው ሦስት ምሁራን ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ደብዳቤ ጻፉ። የባቢሌ ፓርክ ደን ተመንጥሮ ለኢንቨስተሮች መሰጠቱ ከፍተኛ የድርቅ አደጋ እንደሚጋርጥ በመግለጽም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጣልቃ እንዲገቡ ምሁራኑ በደብዳቤያቸው … Read moreContinue Reading
- የበርሊን ማራቶን ባለማዕረግ ትግስት እነ ዱቤ ጂሎ ቢሳተፉ ታዝረከርካቸው ነበርበማራቶን ከሁለት ደቂቃ በላይ ማሻሻል እጅግ የሚደነቅና ያልተለመደ ነው። ባለሙያዎቹ ወይም አሰልጣኞቹ የሮጠችበትን ፍጥነት በሰዓትና ርቀት ከፋፍለው ቢያቀርቡት ምን አልባትም ወንዶችን የሚገዳደር ፍጥነት ተጠቅማ ሮጣለች። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ተቴክኒክ ዳይሬክተርና የአትሌቶች ኮሚሽን ሰብሳቢ የነበሩት የዛሬው የተከበሩ ዱቤ ጅሎ አይነቱን ሯጮችን አዝረክርኮ ማሸነፍ የሚያስችላትን ሃይል አሳይታለች። የበርሊና ባለ ማዕረግ ትዕግስት!! ተግስት … Read moreContinue Reading
- የባህር ዳር ነዋሪዎች- ኢትዮጵያን ዜጎች በሁሉም ቦታ እኩል የሚስተናገዱባት ሀገር ማድረግ ይገባልየባህር ዳር ነዋሪዎች የሕዝብን ጥያቄ የመፍታት አቅም፣ ፍላጎት እና ቅንነት ያለው አመራር በመፍጠር ሕዝብን መካስ እንደሚያስፈልግ፣ ኢትዮጵያ በዘር ከመገፋፋት እና ከመጠቃቃት ነጻ የኾነች ፣ዜጎች በሁሉም ቦታ እኩል የሚስተናገዱባት ሀገር እንድትኾን ማድረግና የፌዴራል መንግሥት የአማራ ሕዝብ ኅብረ ብሔራዊ እና ልማት ወዳድ እንጅ ጦርነትን የማይፈልግ መኾኑን በውል በመገንዘብ የሕዝቡን ተዘዋውሮ የመሥራት እና … Read moreContinue Reading
- ለወልቃይት ጠገዴ ሴቲት ሁመራ አንድ ሚሊዮን የጉልበት ሰራተኛ ይፈለጋል፤ ከአንድ ነጥን አንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ሰሊጥ ይጠበቃል“ከየትኛውም የኢትዮጵያ ክልል አስተማማኝ ሰላም ያለው እዚህ ነው። ለሰራተኞች እንደ ቤተሰብ ዝግጅት አድርገናል። ኑ” ሲሉ የተሰሙት አምስት መቶና ሶስት መቶ ሄክታር ሰሊጥና ማሽላ ያመረቱ ባለሃብቶች ናቸው። የዞኑ ግብርና ቢሮ ሃላፊ እንዳሉት አንድ ሚሊዮን አንድ መቶ ሃምሳ ሁለት ሺህ ኩንታል የሰሊጥ ምርት ስለሚጠበቅ ከአንድ ሚሊዮን በላይ የሰራተኛ ሃይል ያስፈልጋል። የዞኑ አርባ … Read moreContinue Reading