አብዛኞቹ የአፍሪካ ሀገራት ድርጅቶች የመረጃ መረብ ደህንነታቸው የተጠበቀ እንዳልሆነና የፖሊሲ አውጭዎች በትኩረትና በትብብር ሊሰሩ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡የበይነ መረብ ግንኙነት እየጨመረ መምጣት፣ በመረጃ መረብ ደህንነት ላይ በቂ ግንዛቤ አለመኖር፣ ዝቅተኛ የዲጂታል እውቀት፣ የመረጃ መረብ ጥበቃ ባለሙያ እጥረት፣ ፍቃድ የሌላቸው ሶፍትዌሮችን መጠቀም የአፍሪካን የመረጃ መረብ ለመንታፊዎች እንዲጋለጥ አድርጎታል፡፡ ስለሆነም አፍሪካ ምነታፋውን እልባት ለማስያዘ ይቻል ዘነድ በህብረት መስራት እንዳለባት ኢትዮጵያ ጠይቃለች።
ኢትዮጵያ በዓለም አቀፉ የመረጃ መረብ ደህንነት ስብሰባ ላይ አፍሪካዊያን ፖሊሲ አውጭዎች የመረጃ መረብ ደህንነት ላይ በትብብር እንዲሰሩ ጠይቃለች፡፡10ኛው አለም አቀፍ የመረጃ መረብ ደህንነት ስብሰባ-አፍሪካ 2021 በበይነ መረብ እየተካሄደ ነው፡፡
ስብሰባው በመረጃ መረብ ደህንነትና የዲጂታል ጠላፊዎች ላይ ትኩረቱን አድርጎ እየመከረ ነው፡፡የአፍሪካን የመረጃ መረብ ደህንነት ሁኔታ ያብራሩት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ አህመዲን መሃመድ (ፒ ኤች ዲ) አፍሪካ በበይነ መረብ ግንኙነት ተደራሽነት ዝቅተኛ ደረጃ ላይ ብትሆንም በመረጃ መረብ መንታፊዎች በአመት እስከ 3.5 ቢሊየን ዶላር እንደምታጣ ተናግረዋል፡፡
ከሰሃራ በታች ባሉ ሀገራት በ469 ሚሊዮን ገደማ የሞባይል መጠቀሚያዎች 456.3 ቢሊየን ዶላር የገንዘብ ዝውውር እንደሚፈፀም ያብራሩት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ይህ እያደገ የመጣው የሞባይል የገንዘብ ዝውውር የመረጃ መረብ መንታፊዎች አይን ውስጥ እንዲገባ አድርጎታል ብለዋል፡፡
አብዛኞቹ የአፍሪካ ሀገራት ድርጅቶች የመረጃ መረብ ደህንነታቸው የተጠበቀ እንዳልሆነና የፖሊሲ አውጭዎች በትኩረትና በትብብር ሊሰሩ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡የበይነ መረብ ግንኙነት እየጨመረ መምጣት፣ በመረጃ መረብ ደህንነት ላይ በቂ ግንዛቤ አለመኖር፣ ዝቅተኛ የዲጂታል እውቀት፣ የመረጃ መረብ ጥበቃ ባለሙያ እጥረት፣ ፍቃድ የሌላቸው ሶፍትዌሮችን መጠቀም የአፍሪካን የመረጃ መረብ ለመንታፊዎች እንዲጋለጥ አድርጎታል፡፡
ሚኒስትር ዴኤታው፣ ኢትዮጵያን ጨምሮ የአፍሪካን የበይነ መረብ ደህንነት ለማስጠበቅ ከአፍሪካ 2063 አጀንዳ ጋር በተጣጣመ መልኩ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችንም አብራርተዋል፡፡ በሂደት ላይ ያለው የአፍሪካ የአይ ሲ ቲ አድገት ህግና ፖሊሲ፣ የኢንተርኔት መንግስት ሰነድ መዘጋጀቱ፣ የመረጃ መረብ ደህንነትና የግል መረጃ ጥበቃ አዋጅ (ማላቦ ኮንቬንሽን)፣ የመረጃ ደህንነት ዳሰሳ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን መጥቀሳቸውን ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ዓለም አቀፉ የመረጃ መረብ ደህንነት ስብሰባ ትኩረቱን የመረጃ መረብ ደህንነት ላይ አድርጎ በየአመቱ የሚካሄድ ስበሰባ ነው፡፡
- በአሜሪካ ብልጽግናን ተክቶ አራት ኪሎ እንዲገባ ” ዳግማዊ ኢህአዴግ” እንደገና እየተበጀ ነው፤ መንግስት ሙሉ መረጃው አለውበአሜሪካና በተለያዩ አገራት የሚገኙ ስደተኛ ፖለቲከኞች ብልጽግናን በመተካት አራት ኪሎ ለመግባት አሜሪካንን እያባበሉ መሆኑ ተሰማ። እንደ ዜናው ከሆነ አቶ ለማ መገርሳ፣ አቶ ገዱ አንዳርጋቸውና የትህነግ የአሜሪካ ህዋስ አሉበት። ስብስቡ ” ዳግማዊ ኢህአዴግ” የሚል ስም በአንዳንድ ተጋባዦች እየተሰተው ነው። ለውጡን በሙሉ አቅሟ ደግፋ የነበረችው አሜሪካ በቅጽበት የብልጽግናን መንግስትና መሪውን ዶክተር አብይ … Read moreContinue Reading
- ኢዜማ እስር ላይ ያሉት መሪው ዶክተር ጫኔ የድርጅቱን መርህ መጣሳቸውን በይፋ አስታወቀኢዜማ እስር ላይ ያሉት የድርጅቱ መሪ ዶክተር ጫኔ ከበደ የድርጅቱን መርህ መጣሳቸውን በይፋ አስታወቀ። ድርጅቱ ባወጣው መግለጫ ከድርጅቱ መርህ ውጭ ባፈነገጠ መልኩ መንቀሳቀስ ኢዜማን እንደማፍረስ እንደሚቆጠር አስታውቋል። የድርጅቱን መርህና አሰራር የዘርዘረው መግለጫ ” የፓርቲያችን ሊቀመንበር ጉዳይም ከዚህ ከላይ ከተገለፀው መርኅ አንጻር የሚታይ ይሆናል ሲል ፓርቲያችን ይገልፃል” ሲል አቋሙን ይፋ አድርጓል። … Read moreContinue Reading
- የመከላከያን ጨምሮ የአሜሪካንን ሚስጢር “ለትውልድ አገሩ አቀብሏል” የተባለው ትውልደ ኢትዮጵያዊ ” ብሄራዊ ጀግና” እየተባለ ነውባለፉት ሁለት የጦርነት ዓመታት ኢትዮጵያ ላይ የሚያሴሩ፣ ራሳቸውን ሸጠው ኢትዮጵያን የሚያደሙና የቀጠራቸውን አገር ፍላጎት ለማሳካት ውል ገብተው በጋዜጠኛነት ስም ፕሮፓጋንዳ የሚያሰራጩ “ልጆቿን” በገሃድ አይታለች። ዓለም “ታላላቅ” በሚባሉ መሪዎችና ዓለም ዓቀፍ ተቋማት፣ ሚዲያዎች፣ አገራትና ህብረት ስም ኢትዮጵያን ለማወላለቅ ተባብሮ ሲዘምት እነዚሁ ወገኖች አብረው ተሰልፈው ሲያሸረግዱና ለገቡት ውል አፈንድደው የኢትዮጵያን ውድቀት ሲያሳልጡ … Read moreContinue Reading
- በአማራ ክልል ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል፤ “በተፈጠረው የሰላም እጦት ክልሉ ከፍተኛ ገቢ እያጣ ነው”“በተፈጠረው የሰላም እጦት ክልሉ ከፍተኛ ገቢ እያጣ ነው” ሲል የክልሉ ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ አስታወቀ። በክልሉ እየታየ ያለው የሰላም እጦት በኢንቨስትመንቱ ላይ ቀጥተኛ የኾነ ተጽእኖ እያሳደረ እንደኾነ ነው የአማራ ክልል ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ የገለጸው፡፡ እየታየ ያለው አለመረጋጋት ወደ ክልሉ እየገባ ያለውን እና ለመግባት በሂደት ላይ የነበረውን ኢንቨስትመንት እንደሚያስቀር ተገልጿል። … Read moreContinue Reading
- የባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ ለኢንቨስተሮች መሰጠቱን የተቃወሙ ሦስት ምሁራን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ደብዳቤ ጻፉ“እሳቸው ይሄንን ነገር ሰምተውታል ብዬ አላስብም። ከሰሙ እንደሚያስቆሙት እርግጠኛ ነኝ” ከአምስት አስርት ዓመታት በላይ ያስቆጠረው የባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ ከፊል ስፍራ ተቆርሶ ለግብርና ኢንቨስተሮች መሰጠቱ ያስቆጣቸው ሦስት ምሁራን ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ደብዳቤ ጻፉ። የባቢሌ ፓርክ ደን ተመንጥሮ ለኢንቨስተሮች መሰጠቱ ከፍተኛ የድርቅ አደጋ እንደሚጋርጥ በመግለጽም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጣልቃ እንዲገቡ ምሁራኑ በደብዳቤያቸው … Read moreContinue Reading