ኢትዮጵያ ሐሳብን በነፃነት የመግለጽ እና ለፕሬስ ነፃነት መከበር የማይናወጥ አቋም ያላት መሆኑን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታወቀ።
ሐሳብን በነፃነት የመግለጽ እና የፕሬስ ነፃነት መብቶች በሕገ-መንግሥቱ የተረጋገጡ እሴቶች ናቸው ያለው ባለሥልጣኑ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት እነዚህን እሴቶች ለመጠበቅ ቁርጠኛ መሆኑን በድርጊት ያረጋገጠ መሆኑን ጠቁሟል። አሁን በሥልጣን ላይ ያለው መንግሥት ወደ ሥልጣን እንደመጣ በቀዳሚነት የወሰደው እርምጃ ጋዜጠኞችን እና የፖለቲካ እስረኞችን መፍታት እንደነበርም በምሳሌነት አንስቷል።
የውጭም ሆነ የሀገር ውስጥ ጋዜጠኞች የመረጃ ተደራሽነትን እንዲያገኙ ለማስቻልም ለበርካታ ዓመታት ተጥለው የቆዩት ክልከላዎች እና እንቅፋቶች ሙሉ በሙሉ መነሳታቸውንም ጠቅሷል። በአሁኑ ሰዓትም በ129 ቋሚ ዘጋቢዎች የተወከሉ 35 የውጭ የዜና ድርጅቶች ሀገሪቱ ውስጥ እንዳሉም ባለሥልጣኑ ጠቁሟል። ከዚህ ባለፈም በትግራይ ክልል ሲካሄድ በነበረው የሕግ ማስከበር ዘመቻ ወቅትም ከተለያዩ ሀገራት ለተወጣጡ 82 የውጭ ጋዜጠኞች ጊዜያዊ ፈቃድ ተሰጥቶ ያለውን ሁኔታ መዘገብ የሚችሉበት ሁኔታ መመቻቸቱን አመላክቷል።
ሐሳብን በነፃነት የመግለጽ እና የፕሬስ ነፃነት መብቶች በሁሉም ወገኖች መከበር ይኖርባቸዋል ያለው የመገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን፣ ጋዜጠኞቹ የግጭት ዘገባዎችን በተመለከተ ሁኔታውን በሚገልጽ መልኩ ሙያዊ የሆኑ የአዘጋገብ ደንቦችን አክብረው ይዘግባሉ የሚል እምነት እንደነበረው አውስቷል። በየትኛውም ዓለም እንደሚደረገው ሁሉ ወታደራዊ ዘመቻ በሚካሄድበት አካባቢ ገደብ እንደሚጣል በመግለጽም፣ ፈቃድ የተሰጣቸው የውጭ ዘጋቢዎችም ይህንኑ እውነታ አክብረው እና ጠብቀው ይሠራሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልጿል።
ይህ ሳይሆን ቀርቶ የሕግ ጥሰት ሲያጋጥም በየትኛውም የዓለም ክፍል እንደሚደረገው ሁሉ ባለሥልጣኑ ሕግን የማስከበር ኃላፊነቱን የመወጣት ግዴታ እንዳለበት አስገንዝቧል። በዚሁ አግባብ ዓለም አቀፍ ተሞክሮን በመከተል በትብብር ለመሥራት እና ለዘጋቢዎች በተቻለ መጠን ሁኔታዎችን ለማመቻቸት ዝግጁ መሆኑን ባለሥልጣኑ አመልክቷል። አሁንም ቢሆን መንግሥት ሐሳብን በነፃነት የመግለጽ እና የፕሬስ ነፃነትን መከበር በተመለከተ የያዘው አቋም የማይናወጥ መሆኑን ገልጾ፣ “ሀገሪቱም ሆነች ባለሥልጣኑ በቅንነት ሥራቸውን የሚሠሩ ጋዜጠኞችን ለማስተናገድ ዝግጁ ናቸው” ሲል ገልጿል። ( ኢዜአ)
- የባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ ለኢንቨስተሮች መሰጠቱን የተቃወሙ ሦስት ምሁራን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ደብዳቤ ጻፉ“እሳቸው ይሄንን ነገር ሰምተውታል ብዬ አላስብም። ከሰሙ እንደሚያስቆሙት እርግጠኛ ነኝ” ከአምስት አስርት ዓመታት በላይ ያስቆጠረው የባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ ከፊል ስፍራ ተቆርሶ ለግብርና ኢንቨስተሮች መሰጠቱ ያስቆጣቸው ሦስት ምሁራን ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ደብዳቤ ጻፉ። የባቢሌ ፓርክ ደን ተመንጥሮ ለኢንቨስተሮች መሰጠቱ ከፍተኛ የድርቅ አደጋ እንደሚጋርጥ በመግለጽም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጣልቃ እንዲገቡ ምሁራኑ በደብዳቤያቸው … Read moreContinue Reading
- የበርሊን ማራቶን ባለማዕረግ ትግስት እነ ዱቤ ጂሎ ቢሳተፉ ታዝረከርካቸው ነበርበማራቶን ከሁለት ደቂቃ በላይ ማሻሻል እጅግ የሚደነቅና ያልተለመደ ነው። ባለሙያዎቹ ወይም አሰልጣኞቹ የሮጠችበትን ፍጥነት በሰዓትና ርቀት ከፋፍለው ቢያቀርቡት ምን አልባትም ወንዶችን የሚገዳደር ፍጥነት ተጠቅማ ሮጣለች። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ተቴክኒክ ዳይሬክተርና የአትሌቶች ኮሚሽን ሰብሳቢ የነበሩት የዛሬው የተከበሩ ዱቤ ጅሎ አይነቱን ሯጮችን አዝረክርኮ ማሸነፍ የሚያስችላትን ሃይል አሳይታለች። የበርሊና ባለ ማዕረግ ትዕግስት!! ተግስት … Read moreContinue Reading
- የባህር ዳር ነዋሪዎች- ኢትዮጵያን ዜጎች በሁሉም ቦታ እኩል የሚስተናገዱባት ሀገር ማድረግ ይገባልየባህር ዳር ነዋሪዎች የሕዝብን ጥያቄ የመፍታት አቅም፣ ፍላጎት እና ቅንነት ያለው አመራር በመፍጠር ሕዝብን መካስ እንደሚያስፈልግ፣ ኢትዮጵያ በዘር ከመገፋፋት እና ከመጠቃቃት ነጻ የኾነች ፣ዜጎች በሁሉም ቦታ እኩል የሚስተናገዱባት ሀገር እንድትኾን ማድረግና የፌዴራል መንግሥት የአማራ ሕዝብ ኅብረ ብሔራዊ እና ልማት ወዳድ እንጅ ጦርነትን የማይፈልግ መኾኑን በውል በመገንዘብ የሕዝቡን ተዘዋውሮ የመሥራት እና … Read moreContinue Reading
- ለወልቃይት ጠገዴ ሴቲት ሁመራ አንድ ሚሊዮን የጉልበት ሰራተኛ ይፈለጋል፤ ከአንድ ነጥን አንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ሰሊጥ ይጠበቃል“ከየትኛውም የኢትዮጵያ ክልል አስተማማኝ ሰላም ያለው እዚህ ነው። ለሰራተኞች እንደ ቤተሰብ ዝግጅት አድርገናል። ኑ” ሲሉ የተሰሙት አምስት መቶና ሶስት መቶ ሄክታር ሰሊጥና ማሽላ ያመረቱ ባለሃብቶች ናቸው። የዞኑ ግብርና ቢሮ ሃላፊ እንዳሉት አንድ ሚሊዮን አንድ መቶ ሃምሳ ሁለት ሺህ ኩንታል የሰሊጥ ምርት ስለሚጠበቅ ከአንድ ሚሊዮን በላይ የሰራተኛ ሃይል ያስፈልጋል። የዞኑ አርባ … Read moreContinue Reading