ከትግራይ ክልል በስምንት መኪናዎች ተጭኖ በህገ ወጥ መንገድ ሊወጣ የነበረ 800 ኩንታል የዕርዳታ እህል አዲ ጉደም ኬላ ላይ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አሰተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡
በድርጊቱ የተሳተፉ ተጠርጣሪዎችን በህግ ጥላ ስር አድርጎ እያጣራ እንደሚገኝም ኮሚሽኑ ገልጿል። የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አሰተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር መንግስትአብ የማነ ለኢቢሲ እንደገለጹት፤ በክልሉ ለስብዓዊ ድጋፉ የመጣውን የእርዳታ እህል ከተረጂው ሰው ጎሮሮ ቀምተው ለግል ጥቅማቸውና ብልፅግናቸው ሲሯሯጡ የነበሩ ነጋዴዎች ናቸው፡፡
ከእነዚህ ሰዎች ጀርባ የነበሩ እነማን እንደሆኑ ፖሊስ በምርመራ እያጣራ ይገኛል። በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የፀጥታና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ረዳት ኮሚሽነር የማነ ገሰሰው በበኩላቸው ተደራጅተው እህልን ከዚህ አከባቢ በመግዛት ወደ ተለያዩ ቦታዎች በመውሰድ እጥረት በመፍጠር በትግራይ ረሃብና ችግር እንዲፈጠር የሚያደርጉ አካላት መኖናረቸውን ገልጸዋል፡፡
የወንጀል አፈጻጸሙ በተደራጀ መንገድ መሆኑንም የገለጹት ረዳት ኮሚሽነሩ፤ በዚህ ህገ ወጥ ድርጊት ውስጥ በየዋህነት የሚሳተፉ ባለሞያዎች ጥንቃቄ እንዲያደርጉም አሳስበዋል፡፡ ከዚህ በፊት በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረው ሶስት ሺህ ኩንታል የእርዳታ ዕህል መያዙን የገለጸው ፖሊስ በወንጀል ድርጊቱ የተሳተፉ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ሆነው ምርመራ እየተደረገባቸው ይገኛል፡፡
እንደ ኮሚሽነሩ ገለጻ፣ ከዚህ የከፋ ችግር ስለሌለ ህብረተሰቡ በንቃት መሳተፍ ይኖርበታል፡፡ ከህገ ወጥና ስግብግብ ነዳዴዎች በስተጀርባ ያለ ማንኛውም አካል ከህግ ተጠያቂነት እንደማያመልጥ ማወቅ ይኖርበታል ብለዋል፡፡ የመቀለ ከተማ ጊዜያዊ አስተዳደር ከንቲባ ኢንጂነር ግዛው ሐጎስ በበኩላቸው፣ ይህ ህገ ወጥ ተግባር በመጀመሪያው እርዳታ አሰጣጥ ላይ መከሰቱን ጠቅሰው በሁለተኛው ዙር ላይ ይሄ እንዳይደገም በጥብቅ ቁጥጥር እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል።
- የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነትና ወሰን አስመላሽ ኮሚቴ ለትግራይ ሕዝብ ጥሪ አቀረበ፤ “አማራ ልዩነትህን ወደጎን አድርግ፤ዳግም በጅምላ አንቀበርም”“የትግል አደራ አይታጠፍም፤ ዳግም በጅምላ አንገደልም!” በሚል ርዕስ የወልቃይት ጠገዴ… Read more: የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነትና ወሰን አስመላሽ ኮሚቴ ለትግራይ ሕዝብ ጥሪ አቀረበ፤ “አማራ ልዩነትህን ወደጎን አድርግ፤ዳግም በጅምላ አንቀበርም”
- በዝቋላ ገዳም የሆነው ይህ ነው!!More stories ዐቢይ አሕመድ ከትግራይ ህዝብ ተወካዮች ጋርApril 1, 2024… Read more: በዝቋላ ገዳም የሆነው ይህ ነው!!
- Kenya’s military chief dies in a helicopter crash, Nairobi declares three days of national mourningKenya’s military chief Gen. Francis Ogolla died in a helicopter… Read more: Kenya’s military chief dies in a helicopter crash, Nairobi declares three days of national mourning
- U.S. stops UN from recognizing a Palestinian state through membershipCGTN – The United States on Thursday stopped the UN… Read more: U.S. stops UN from recognizing a Palestinian state through membership
- Israel launches missile attacks on Iran: reportCGTN – Israeli missiles have hit a site in Iran,… Read more: Israel launches missile attacks on Iran: report