የአገር መከላከያ ሰራዊት ለምርጫና ለሁለለተኛው የህዳሴ ግድብ ሙሌት እንከን እንዳይፈጠር በጥብቅ ዝግጅት ማድረጉ ተገለጸ። የምድርና የአየር ሃይል አዛዦች በተደጋጋሚ ይህንን ቢሉም ዛሬ በድጋሚ ኮሎኔል ጌትነት አዳነ ይህንኑ አጠንከረው አስታውቀዋል። በምርጫ ዙሪያ ወንጀል የሰሩም ተያዘዋል።
የመከላከያ ሚኒስቴርም ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩሉን ድርሻ እንደሚወጣ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮሎኔል ጌትነት የተናገሩት ለአሐዱ ሬዲዮ ነው። 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ የመከላከያ ሰራዊት ዝግጅት አድርጓል ነው ያሉት።
” በመላው ሀገሪቱ ወንጀለኛን አድኖ ለመያዝ የመከላከያ ሰራዊቱ ዝግጁ ነው” ሲሉ ያስታወቁት ኮሎኔሉ በተለይ ስለተደረገው ዝግጅት ማብራሪያ አልሰጡም።
ኢትዮጵያ 6ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ለማካሄድ ቀን መቁረጧ ይታወቃል፡፡ ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ዝግጅት እያደረጉ ስለመሆኑ በየፊናቸው ከሚሰጡት መረጃ ለመረዳት ተችሏል። ብልጽግናም ስብሰባውን ሲያጠቃልል ምርጫው መሰላማዊ እንዲጠናቀቅ፣ ሁለተኛው የውሃ ሙሌት በተሳካ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን ሁሉ ለማድረግ አቋም መያዛቸው ይታውሳል። ላለፉት አራት ወራት ቁጥራቸው በውል ያልተገለጸ የፖሊስ አባላት፣ በልዩ ልዩ ስልታዊ ተግባር የሰለጠኑ፣ ከፖሊስ ኮሌጅ የወጡ መኮንኖች በተከታታይ ሲመረቁ በክልል ደረጃም ሰፊ ቁጥር ያለው ሃይል ወደ ስራ መግባቱ ይታወሳል።
በለኢላ የምርጫ ዜና የምርጫ ቅስቀሳ ባነር ወይም የምርጫ ምልክት በመቅደድ የተጠረጠሩ 22 ግለሰቦችን በመያዝ እያጣራሁ ነዉ ሲል የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮምሽን አስታወቋል።
ስድስተኛዉ ሀገራዊ ምርጫ በሰላማዊ መንገድ እንዲጠናቀቅ እየሰራሁ ነዉ ያለዉ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮምሽን የፖለቲካ ፓርቲዎች የቅስቀሳ ባነሮችን ቀደዋል ተብለዉ የተጠረጠሩ 22 ግለሰቦችን መያዙን ገልፃል፡፡
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮምሽን የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮማንደር ፋሲካ ፈንታ እንደተናገሩት በከተማዋ ስድስተኛዉን ሀገራዊ ምርጫ ለማካሄድ የተሰቀሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ባነርን በመቅደድ የተጠረጠሩ ግለሰቦችን መያዙን ገልፀዉ ከነዚህ ዉስጥ በኮልፌ ቀራንዮ አንድ ግለሰብ የ5 ወር እስራት ተፈርዶበታል ሲሉ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡
ኮማንደሩ አክለዉም የዘንድሮዉ ስድስተኛዉ ሀገራዊ ምርጫ ከዚህ በፊት ከተካሄዱ አምስት ሀገራዊ ምርጫዎች የተሻለ እና የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ከዚህ ቀደም ከነበሩ ምርጫዎች በተሻለ የምርጫ ምልክታቸዉን በነፃነት እያስተዋወቁ ነዉ ሲሉ ጨምረዉ ገልፀዋል፡፡
- ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በከፍተኛ የውስጥ ችግር ውስጥ ናት፤ በጾሙ ማቅ ለብሰው በንስሃ ችግራቸውን ይፍቱየኢትዮጵያ ታሪክ ቁንጮ እንደሆነች የሚመሰከርላትና እጅግ ውብ ስብዕና ያላቸው አባቶች የሚጠቀሱላት ዕድሜ ጠገብቷ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በከፍተኛ የውስጥ… Read more: ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በከፍተኛ የውስጥ ችግር ውስጥ ናት፤ በጾሙ ማቅ ለብሰው በንስሃ ችግራቸውን ይፍቱ
- ሕብረቱ ከታገዱ የሩሲያ ንብረቶች የሚገኘውን ትርፍ ለዩክሬን ጦር መሳሪያ ግዢ ሊያውል ነውየአውሮፓ ሕብረት በአባል ሀገራቱ እንዳይንቀሳቀሱ ከታገዱ የሩሲያ ንብረቶች የሚገኘውን ትርፍ ዩክሬንን ጦር መሳሪያ ለማስታጠቅ ሊያውል መሆኑ ተሰምቷል፡፡ More… Read more: ሕብረቱ ከታገዱ የሩሲያ ንብረቶች የሚገኘውን ትርፍ ለዩክሬን ጦር መሳሪያ ግዢ ሊያውል ነው
- ሳኡዲ የምታስገነባው አዲስ ከተማ – “ኒዮም ሲቲ” (Neom City)በረሃን ወደ ከተማነት የመቀየር ጥበብ ልንለው እንችላለን፡፡ ከ1 ትሪሊየን ዶላር በላይ የሚፈጅ ውድ ሥራም ነው፡፡ ከገንዘቡ ባሻገር ብዙ… Read more: ሳኡዲ የምታስገነባው አዲስ ከተማ – “ኒዮም ሲቲ” (Neom City)
- Ethiopia, Somalia dispute won’t transform into turmoil for the Horn of Africadeal between Ethiopia and Somaliland has sent waves of debates throughout the region, has even raised questions about… Read more: Ethiopia, Somalia dispute won’t transform into turmoil for the Horn of Africa
- በአማራና ትግራይ ክልል ያሉ የወሰን ይገባኛል ጥያቄ በህዝብ ውሳኔ እንዲቋጭ ስምምነት ተደረሰትህነግ በበላይነት የሚመራው ኢህአዴግ ከፈርሰ በሁዋላ የተነሳውን ጦርነት ተከትሎ የአማራ ክልል ” ነጻ ወጡ” ባላቸው አካባቢዎች ለዓመታት የቆየ… Read more: በአማራና ትግራይ ክልል ያሉ የወሰን ይገባኛል ጥያቄ በህዝብ ውሳኔ እንዲቋጭ ስምምነት ተደረሰ