የአገር መከላከያ ሰራዊት ለምርጫና ለሁለለተኛው የህዳሴ ግድብ ሙሌት እንከን እንዳይፈጠር በጥብቅ ዝግጅት ማድረጉ ተገለጸ። የምድርና የአየር ሃይል አዛዦች በተደጋጋሚ ይህንን ቢሉም ዛሬ በድጋሚ ኮሎኔል ጌትነት አዳነ ይህንኑ አጠንከረው አስታውቀዋል። በምርጫ ዙሪያ ወንጀል የሰሩም ተያዘዋል።
የመከላከያ ሚኒስቴርም ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩሉን ድርሻ እንደሚወጣ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮሎኔል ጌትነት የተናገሩት ለአሐዱ ሬዲዮ ነው። 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ የመከላከያ ሰራዊት ዝግጅት አድርጓል ነው ያሉት።
” በመላው ሀገሪቱ ወንጀለኛን አድኖ ለመያዝ የመከላከያ ሰራዊቱ ዝግጁ ነው” ሲሉ ያስታወቁት ኮሎኔሉ በተለይ ስለተደረገው ዝግጅት ማብራሪያ አልሰጡም።
ኢትዮጵያ 6ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ለማካሄድ ቀን መቁረጧ ይታወቃል፡፡ ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ዝግጅት እያደረጉ ስለመሆኑ በየፊናቸው ከሚሰጡት መረጃ ለመረዳት ተችሏል። ብልጽግናም ስብሰባውን ሲያጠቃልል ምርጫው መሰላማዊ እንዲጠናቀቅ፣ ሁለተኛው የውሃ ሙሌት በተሳካ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን ሁሉ ለማድረግ አቋም መያዛቸው ይታውሳል። ላለፉት አራት ወራት ቁጥራቸው በውል ያልተገለጸ የፖሊስ አባላት፣ በልዩ ልዩ ስልታዊ ተግባር የሰለጠኑ፣ ከፖሊስ ኮሌጅ የወጡ መኮንኖች በተከታታይ ሲመረቁ በክልል ደረጃም ሰፊ ቁጥር ያለው ሃይል ወደ ስራ መግባቱ ይታወሳል።
በለኢላ የምርጫ ዜና የምርጫ ቅስቀሳ ባነር ወይም የምርጫ ምልክት በመቅደድ የተጠረጠሩ 22 ግለሰቦችን በመያዝ እያጣራሁ ነዉ ሲል የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮምሽን አስታወቋል።
ስድስተኛዉ ሀገራዊ ምርጫ በሰላማዊ መንገድ እንዲጠናቀቅ እየሰራሁ ነዉ ያለዉ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮምሽን የፖለቲካ ፓርቲዎች የቅስቀሳ ባነሮችን ቀደዋል ተብለዉ የተጠረጠሩ 22 ግለሰቦችን መያዙን ገልፃል፡፡
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮምሽን የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮማንደር ፋሲካ ፈንታ እንደተናገሩት በከተማዋ ስድስተኛዉን ሀገራዊ ምርጫ ለማካሄድ የተሰቀሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ባነርን በመቅደድ የተጠረጠሩ ግለሰቦችን መያዙን ገልፀዉ ከነዚህ ዉስጥ በኮልፌ ቀራንዮ አንድ ግለሰብ የ5 ወር እስራት ተፈርዶበታል ሲሉ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡
ኮማንደሩ አክለዉም የዘንድሮዉ ስድስተኛዉ ሀገራዊ ምርጫ ከዚህ በፊት ከተካሄዱ አምስት ሀገራዊ ምርጫዎች የተሻለ እና የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ከዚህ ቀደም ከነበሩ ምርጫዎች በተሻለ የምርጫ ምልክታቸዉን በነፃነት እያስተዋወቁ ነዉ ሲሉ ጨምረዉ ገልፀዋል፡፡
- አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎችባንኩ የክፍያ ሰነድ ቀረበለት። ማጣሪያ ጥያቄ ለህብረቱ አቀረበ። ሃሰት ሆኖ ተገኘና ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን ያዘ። ጉዳዩ ወደ ህግ አመራ።… Read more: አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎች
- የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል 300 ቢሊዮን ብር የንግድ ባንክ ዕዳ አለብኝ አለ፤ ዕዳውና የክፍያው ጫና እንደከበደውም አስታውቋልየኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከንግድ ባንክ 300 ቢሊዮን ብር ዕዳ እንዳለበት ተገለጸ። የዕዳ ጫናውን ለማቃለል የባንክ ወልዱም ጭምር ተፅእኖ… Read more: የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል 300 ቢሊዮን ብር የንግድ ባንክ ዕዳ አለብኝ አለ፤ ዕዳውና የክፍያው ጫና እንደከበደውም አስታውቋል
- ዋና ዋና የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ይዘቶች – ሲጨመቁመግቢያ ሽግግር ፍትህ ጉልህ የመብት ጥሰቶች በተፈፀመባቸው ሀገራት ተጠያቂነትን ለማስፈን እና ተበዳዮችን ለመካስ ጥቅም ላይ ሲውል ቆይቷል፡፡ በሀገራችንም… Read more: ዋና ዋና የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ይዘቶች – ሲጨመቁ
- “የአማራ ክልል ሚሊሻዎች ትጥቅ ይፍቱ በሚል የሚሰራጩ መረጃዎች ‘ባልበላውም ጭሬ ላፍሰው’ ከሚል ቅዠት የተወለደ ቅጥፈት ነው”“የሚሊሻ ኀይሉን በተመለከተ የሚዘዋወረው መረጃ ፍጹም መሠረተ ቢስ ነው” ሲሉ ኮሎኔል ግርማ ገሰሰ አስታወቁ። “ቅጥፈት ነው” ያሉትና በፕሬዚዳንቱ… Read more: “የአማራ ክልል ሚሊሻዎች ትጥቅ ይፍቱ በሚል የሚሰራጩ መረጃዎች ‘ባልበላውም ጭሬ ላፍሰው’ ከሚል ቅዠት የተወለደ ቅጥፈት ነው”
- “የህዝባችንን ድምጽ የሚቀማና የሚያፍን የ’አማራ ስብስብ’ ለአማራ ክልል ተግዳሮት ሆኗል… ትህነግ ዘርፎ እያጋጋዘ ነው” አብን“የትግራይ ተወላጆች ትህነግ ለፈጸመው ወረራ፣ ዘረፋ፣ ማፈናቀልና የግድያ ተግባራት የተቀናጀ የፖለቲካና የሚዲያ ድጋፍ ሰጥተዋል። በተለይም በትግራይ ክልል መቀሌ… Read more: “የህዝባችንን ድምጽ የሚቀማና የሚያፍን የ’አማራ ስብስብ’ ለአማራ ክልል ተግዳሮት ሆኗል… ትህነግ ዘርፎ እያጋጋዘ ነው” አብን