ከአማራ ክልል ከተለያዩ ዞኖች በደላሎች ተታለው በህገ ወጥ መንገድ ከሃገር ለመውጣት የሞከሩ 60 ወጣቶች መያዛቸውን ፖሊስ አስታወቀ።
በአማራ ክልል በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን የባቲ ከተማ ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር መሃመድ አሊ ለኢዜአ እንደገለጹት ወጣቶቹ ጨለማን ተገን አድርገው ከሃገር ለመውጣት ሲሞክሩ ትላንት ከለሊቱ ዘጠኝ ሰዓት ላይ በባቲ ከተማ ተይዘዋል ።
ወጣቶቹ በህገ ወጥ መንገድ ወደ አረብ ሀገር ለመውጣት የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3- 43619 አአ በሆነ የጭነት አይሱዙ ተሽከርካሪ ተሳፍረው ከደጋን መስመር ወደ አፋር በመጓዝ ላይ እንዳሉ በከተማው ቀበሌ 03 ቀርሳ ፍተሻ ጣቢያ ላይ መያዛቸውን ተናግረዋል ።
ወጣቶቹ ከ17 እስከ 28 ዓመት የእድሜ ክልል ውስጥ ያሉ መሆናቸውን ጠቁመው ከወጣቶቹ መካከል ሶስቱ ሴቶች እንደሆኑ ገልጸዋል።
እንደ ዋና ኢኒስፔክተሩ ገለጻ ወጣቶቹ ከሰሜን ወሎ፣ ደቡብ ወሎ፣ ሰሜን ሽዋና ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞኖች በህገ ወጥ ደላሎች ተታለው የተሰባሰቡ መሆናቸውን አመልክተዋል።
ወጣቶቹን በህገወጥ መንገድ ከሀገር ለማሶጣት በታሰበ ወንጀል ተሳትፎ እንዳላቸው የተጠረጠሩ አሽከርካሪውን ጨምሮ ሁለት ግለሰቦች ተሸከርካሪውን አቁመው መሰወራቸውን ተናግረዋል ።
ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ስር ለማዋል ክትትል መጀመሩን አመልክተዋል ።
ወጣቶቹን በሂደት ወደ አካባቢያቸው ለመመለስ ከወዲሁ ስራዎች መጀመራቸውንም ጠቁመዋል።
ዜጎች ጫካ ለጫካ ጭምር በእግራቸው በመጓዝ በህገ ወጥ መንገድ ወደ ውጭ ሀገራት ለመውጣት በሚያደርጉት ሙከራ ለሞት፣ ለአካል ጉዳትና ለመደፈር እየተጋለጡ መሆናቸውን አብራርተዋል።
ድርጊቱ በተደራጀ አግባብ የሚፈፀም በመሆኑ ለመከላከል አስቸጋሪ እንዳደረገው ያመለከቱት ዋና ኢኒስፔክተሩ የባለድርሻ አካላት ጠንካራ ትብብር በመፍጠር ድርጊቱን ለመከላከል ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል ። via (ኢዜአ)
- ዋና ዋና የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ይዘቶች – ሲጨመቁመግቢያ ሽግግር ፍትህ ጉልህ የመብት ጥሰቶች በተፈፀመባቸው ሀገራት ተጠያቂነትን ለማስፈን እና ተበዳዮችን ለመካስ ጥቅም ላይ ሲውል ቆይቷል፡፡… Read more: ዋና ዋና የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ይዘቶች – ሲጨመቁ
- “የአማራ ክልል ሚሊሻዎች ትጥቅ ይፍቱ በሚል የሚሰራጩ መረጃዎች ‘ባልበላውም ጭሬ ላፍሰው’ ከሚል ቅዠት የተወለደ ቅጥፈት ነው”“የሚሊሻ ኀይሉን በተመለከተ የሚዘዋወረው መረጃ ፍጹም መሠረተ ቢስ ነው” ሲሉ ኮሎኔል ግርማ ገሰሰ አስታወቁ። “ቅጥፈት ነው” ያሉትና… Read more: “የአማራ ክልል ሚሊሻዎች ትጥቅ ይፍቱ በሚል የሚሰራጩ መረጃዎች ‘ባልበላውም ጭሬ ላፍሰው’ ከሚል ቅዠት የተወለደ ቅጥፈት ነው”
- “የህዝባችንን ድምጽ የሚቀማና የሚያፍን የ’አማራ ስብስብ’ ለአማራ ክልል ተግዳሮት ሆኗል… ትህነግ ዘርፎ እያጋጋዘ ነው” አብን“የትግራይ ተወላጆች ትህነግ ለፈጸመው ወረራ፣ ዘረፋ፣ ማፈናቀልና የግድያ ተግባራት የተቀናጀ የፖለቲካና የሚዲያ ድጋፍ ሰጥተዋል። በተለይም በትግራይ ክልል… Read more: “የህዝባችንን ድምጽ የሚቀማና የሚያፍን የ’አማራ ስብስብ’ ለአማራ ክልል ተግዳሮት ሆኗል… ትህነግ ዘርፎ እያጋጋዘ ነው” አብን
- የዜናው ሰም፣ ወርቅና “ትህነግ ብልፅግናን ለመቀላቀል በድርድር ላይ ነው ” የትህነግ ዜናውን አጣጣለለአንድ ቀን ከጮኸና አየሩን ሁሉ ከተቆጣጠረ በሁዋላ ውሃ የተቸለሰበት “ሕወሓት ብልፅግናን ለመቀላቀል በድርድር ላይ ነው” የሚለው የዋዜማ… Read more: የዜናው ሰም፣ ወርቅና “ትህነግ ብልፅግናን ለመቀላቀል በድርድር ላይ ነው ” የትህነግ ዜናውን አጣጣለ
- National Dialogue, Transitional Justice And Rehabilitation Process Pillars of Lasting Peace, Prosperity: CouncilThe Ethiopian National Security Council has issued a statement on latest developments in the country. In its… Read more: National Dialogue, Transitional Justice And Rehabilitation Process Pillars of Lasting Peace, Prosperity: Council