\ስድስተኛውን አጠቃላይ አገራዊ ምርጫ የሚታዘቡ የአፍሪካ ሕብረት የረጅም ጊዜ የምርጫ ታዛቢዎች አዲስ አበባ መግባታቸው ተገለጸ። የሕብረቱ የአጭር ጊዜ ታዛቢዎች ከምርጫው አንድ ሳምንት በፊት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጡም ተገልጿል። በቅድመ ምርጫ ግምገማ የተሰማሩ ጉዟቸውን አጠናቀው ከምርጫ ቦርድ ጋር የመጨረሻ ውይይት ያደርጋሉ።
የኢትዮጵያ መንግስት ያቀረበውን ግብዣ ተከትሎ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ሙሳ ፋቂ ማህማት ምርጫውን የሚታዘቡ የአፍሪካ ሕብረት የአጭርና የረጅም ጊዜ ታዛቢዎችን ስምሪት ማድነቃቸው ይታወሳል።
ሕብረቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ ከሕብረቱ አባል አገራት የተውጣጡ ስምንት አባላት ያሉት የረጅም ጊዜ የምርጫ ታዛቢዎች ቡድን ግንቦት 25 እና 26 ቀን 2013 ዓ.ም አዲስ አበባ መግባቱን ገልጿል።
ታዛቢዎቹ በአጠቃላይ ምርጫ ሂደቱ ያለው የፖለቲካ ከባቢ አየር፣ የምርጫው ሕጋዊ ማዕቀፎች፣ የምርጫ ዝግጅትና አስተዳደር ግልጽነትና ውጤታማነት፣ የምርጫ ቅስቅሳ ሁኔታ የመታዘብ ስራ እንደሚያከናውኑም ተጠቅሷል።
ይህ በንዲህ እንዳለ ለቅድመ ምርጫ ግምገማ ወደ ኢትዮጵያ ያቀኑት ተቋማት ቅድመ ምልከታቸውን አጠናቀው ሪፖርታቸውን ለማቅረብ ዛሬ ከምርጫ ቦርድ ጋር የሪፖርት ማሟያ ውይይት እንደሚያደርጉ ተሰምቷል። የኢትይ 12 የአዲስ አበባ ተባባሪ እንዳለው በቅድም ግምገማው ይህ ነው የሚባል የነቀፌታ ችግር እንዳልተገኘ ስራውን እየሰሩ ካሉ ሰምቷል።
አብዛኛው ሕዝብ ምርጫው ተደርጎ መገላገል እንደሚፈልግ፣ ከምርቻው በሁዋላ ሰፊ ተስፋ እንዳላቸውና የምርጫው መጠናቀቅ በጉልህ እንደሚያጠባበቁ የተሰበሰቡ አስተያየቶች እንደሚጠቁሙ የወሬው ምንጮች ገልጸዋል። በአንዳንድ ቦታዎች ረብሻ ይነሳል የሚል ስጋት ያላቸው ቢኖሩም ማን? ለምን? እንዴትና? የት ረብሻ እንደሚያደርግ አያውቁም። በወሬ ደረጃ ግን ሰዎችን የሚያስጨንቁ አሉ።
በብልጽግና ፓርቲ አመራሮች ዘንድ ስጋት እንደማይታይ ታዛቢዎቹ ተረድተዋል። አብዛኞቹ በተዘዋወሩባቸው ስፍራዎች ህዝብ የኮሮና ስጋት እንደሌለበት፤ ለስጋት የሚዳርግ ምንም ጉዳይ አለመኖሩን አይተዋል። ምርጫ ቦርድ ስጋት አለባቸውን ያላቸውን ስፍራዎች በአማራ ክልልና በኦሮሚያ ምርጫ እንዳይካሄድባቸው መወሰኑ ይታወሳል።
- የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነትና ወሰን አስመላሽ ኮሚቴ ለትግራይ ሕዝብ ጥሪ አቀረበ፤ “አማራ ልዩነትህን ወደጎን አድርግ፤ዳግም በጅምላ አንቀበርም”“የትግል አደራ አይታጠፍም፤ ዳግም በጅምላ አንገደልም!” በሚል ርዕስ የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነትና ወሰን አስመላሽ ኮሚቴ ባሰራጨው… Read more: የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነትና ወሰን አስመላሽ ኮሚቴ ለትግራይ ሕዝብ ጥሪ አቀረበ፤ “አማራ ልዩነትህን ወደጎን አድርግ፤ዳግም በጅምላ አንቀበርም”
- በዝቋላ ገዳም የሆነው ይህ ነው!!More stories የባህር በር ህልውናችን!! አብይ አህመድ “መተንፈሻ ወደብ ያስፈልገናል” ሲሉ አወጁDecember 30, 2023 ዐቢይ አሕመድ… Read more: በዝቋላ ገዳም የሆነው ይህ ነው!!
- Kenya’s military chief dies in a helicopter crash, Nairobi declares three days of national mourningKenya’s military chief Gen. Francis Ogolla died in a helicopter crash west of the country, President… Read more: Kenya’s military chief dies in a helicopter crash, Nairobi declares three days of national mourning
- U.S. stops UN from recognizing a Palestinian state through membershipCGTN – The United States on Thursday stopped the UN from recognizing a Palestinian state by… Read more: U.S. stops UN from recognizing a Palestinian state through membership
- Israel launches missile attacks on Iran: reportCGTN – Israeli missiles have hit a site in Iran, ABC News reported late on Thursday,… Read more: Israel launches missile attacks on Iran: report