ከ15 ወራት በላይ ስጋት ሆኖ የዘለቀው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ 36 የጤና ባለሙያዎችን ህይወት እንደነጠቀ የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቀ።በቫይረሱ 3 ሺህ 329 የጤና ባለሙያዎች ተይዘው እንደነበር እና ከነዚህም ውስጥ 36ቱ ህይወታቸው ማለፉን የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ አስቻለሁ አባይነህ ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ በአጠቃላይ እስከ ሰኔ ሶስት ባለው ጊዜ በቫይረሱ ምክንያት 4 ሺህ 226 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል ተብሏል።ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ ይህን ያሉት የጤና ሚኒስቴር ከሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመሆን ሐገራዊ የወረርሽኙን ስርጭት የሚያመላክተቱ ጥናቶች የሚቀርቡበት መድረክ ላይ ነው።
ወረርሽኙ ከባድ ጫና በሀገር ላይ ፈጥሯል ያሉት አቶ አባይነህ፣ የኮቪድ 19 ወረርሽኝን ለመከላከል የተወሰዱ እርምጃዎች በቫይረሱ ምክንያት ሊደርስ የሚችለውን የሞት መጠን መቀነስ እንዳስቻለም ጠቁመዋል።ምክትል ዳይክተሩ ወረርሽኙ ሲጀምር ምንም አይነት የመርመሪያ መሳሪያ ያልነበረ ሲሆን አሁን ላይ 82 የመንግስትንና የግል የላብራቶሪ ተቋማት የኮቪድ ምርመራ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑንም ተናግረዋል።
የምርመራ ኪትም በሀገር ውስጥ እየተመረተ እንዳለ እና ይህም በውጭ ምንዛሬ እጥረት ይስተጓጎል የነበረውን የግዥ ሒደት ማስቀረት እንዳስቻለ ተነግሯል።የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚንስትር ዴኤታ ዶክተር ሙሉ ነጋ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አዳዲስ ሃሳቦችን በማፍለቅ ወረርሽኙን ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት እያገዙ መሆናቸውን ተናግረዋል።በቀጣይም በወረርሽኙ ምክንያት ሊደርስ የሚችለውን ጉዳት ለመቀነስ ጥንቃቄዎች ሊደረጉ ይገባል ተብሏል።
ኢቢሲ ዜና
- Somaliland offended by G7 referring the Republic of Somaliland as “Somaliland Region of Somalia” The Republic of Somaliland, is a sovereign state with its own laws and constitution, reaffirmed by the people… Read more: Somaliland offended by G7 referring the Republic of Somaliland as “Somaliland Region of Somalia”
- ” በትጥቅ ትግል ውስጥ ያሉ ወገኖቻችን አሁንም ሳይመሽ ቶሎ ወደ ድርድሩ እንዲገቡ በትህትና እንጠይቃለን ” ፕ/ር መስፍን አርአያየኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በሌላ መንገድ እየታገሉ ይገኛሉ ያላቸው አካላት ወደ ምክክር መድረኩ እንዲገቡ ጥሪ አቀረበ። ኮሚሽኑ ከዚህ… Read more: ” በትጥቅ ትግል ውስጥ ያሉ ወገኖቻችን አሁንም ሳይመሽ ቶሎ ወደ ድርድሩ እንዲገቡ በትህትና እንጠይቃለን ” ፕ/ር መስፍን አርአያ
- የቡድን ሰባት አገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በኢትዮጵያ ጉዳይ የይሁንታና የስጋት ቅልቅል መግለጫ ሰጡየቡድን ሰባት ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በተለያዩ ጉዳዮች ላይ መግለጫ ሲሰጡ እግረመንገዳቸውን ኢትዮጵያን አስመልክቶ በበጎ ጎኑንና በስጋት ከፍለው… Read more: የቡድን ሰባት አገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በኢትዮጵያ ጉዳይ የይሁንታና የስጋት ቅልቅል መግለጫ ሰጡ
- Foreign firms’ local market involvement entails economic dynamismPermitting foreign firm’s involvement in the import, wholesale and retail business, which was restricted to local companies, would… Read more: Foreign firms’ local market involvement entails economic dynamism