አቶ ደመቀ መኮንን ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሃላፊነታቸው በተጨማሪ ደርበው እየሰሩ ላሉበት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቦታ የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሙስጣፌ መታጨታቸው ተሰማ። ክልሉና በውጭ አገር ያሉ የክልሉ ተወላጆች በዜናው ደስተኛ አይደሉም።
የአብዲሌ ወንበር ላይ ከተቀመጡ ጀምሮ እጅግ በሚገርም ሁኔታ በመላው አገሪቱ ተቀባይነት ያገኙት ሙስጣፌ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርነት የታጩት ገዢው ፓርቲ ብልጽግና በምርጫው ካሸነፈ አዲስ በሚዋቀረው ካቢኔ የሚካተቱ እንዲሆን ታስቦ ነው።
በሚመሩት ክልል ሁሉም ብሄረሰቦች እኩል ሆነው የሚስተናገዱበትን፣ ቋንቋውን ከቻሉ በሃላፊነት የሚመደቡበትንና ልዩነት የሌለበትን አሰራር በማስፈን ሰላም ያወረዱት ሙስጣፌ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እንዲሆን መታጨታቸውን አስመልክቶ የክልሉን ተወላጅ ዲያስፖራ አባላትን አናገረን ቅሬታቸውን ገልጸዋል።
የሜኖሶታ ነዋሪ የሆኑ የሶማሌ ተወላጅ ” ዜናውን ሰምተናል፤ ደስተኛ አይደለንም” ብለዋል። በሙስጣፌ ሹመት ሳይሆን ክልሉ ላይ የጀመሩትን ተግባር እንዲያጠናክሩ ከመመኘት አንጻር ባሉበት እንዲቀጥሉ ምኞታቸው እንደሆነም አስታውቀዋል። ክልሉ አካባቢም ተመሳሳይ እምነት እንዳለ ለማወቅ ችለናል።
በሌላ ዜና የሜኖሶታ ነዋሪ የሶማሌ ተወላጆች አሁን አሜሪካ ኢትዮጵያ ላይ የያዝቸውን አቋም እንዲላዘብ እየሰሩ መሆናቸው ታውቋል። ሰፊ የሶማሌና የኦሮሞ ማህበረሰብ ባለበት ሚኖሶታ የሶማሌ ድምጽና ተጽዕኖ ከፍተኛ በመሆኑ በአካባቢው ያሉትን ሴናተር ማሳመናቸውም ታውቋል። ትናት ወደ ሜኖሶታ ያቀናው የክልሉ ሉዑል ቡድን ከባለስልታኑ ጋር እንዲገናኝ መመቻቸቱንም ጠቁመውናል።
ሙስጣፊ በትህነግና በትህነግ ደጋፊዎች ዘንድ ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ቀጥለው የሚጠሉ፣ በመላው አገሪቱ ደግሞ ተቀባይነትን ያገኙ የለውጡ ቱርፋት የሆኑ አዲስ መሪ መሆናቸው ይታወቃል።
- “የአማራ ክልል ሚሊሻዎች ትጥቅ ይፍቱ በሚል የሚሰራጩ መረጃዎች ‘ባልበላውም ጭሬ ላፍሰው’ ከሚል ቅዠት የተወለደ ቅጥፈት ነው”“የሚሊሻ ኀይሉን በተመለከተ የሚዘዋወረው መረጃ ፍጹም መሠረተ ቢስ ነው” ሲሉ ኮሎኔል ግርማ ገሰሰ አስታወቁ። “ቅጥፈት ነው” ያሉትና… Read more: “የአማራ ክልል ሚሊሻዎች ትጥቅ ይፍቱ በሚል የሚሰራጩ መረጃዎች ‘ባልበላውም ጭሬ ላፍሰው’ ከሚል ቅዠት የተወለደ ቅጥፈት ነው”
- “የህዝባችንን ድምጽ የሚቀማና የሚያፍን የ’አማራ ስብስብ’ ለአማራ ክልል ተግዳሮት ሆኗል… ትህነግ ዘርፎ እያጋጋዘ ነው” አብን“የትግራይ ተወላጆች ትህነግ ለፈጸመው ወረራ፣ ዘረፋ፣ ማፈናቀልና የግድያ ተግባራት የተቀናጀ የፖለቲካና የሚዲያ ድጋፍ ሰጥተዋል። በተለይም በትግራይ ክልል… Read more: “የህዝባችንን ድምጽ የሚቀማና የሚያፍን የ’አማራ ስብስብ’ ለአማራ ክልል ተግዳሮት ሆኗል… ትህነግ ዘርፎ እያጋጋዘ ነው” አብን
- “ትህነግ ብልፅግናን ለመቀላቀል በድርድር ላይ ነው ” የዜናው ሰም፣ ወርቅና የትህነግ ‘ ሃሰት ነው’ ማስተባበያለአንድ ቀን ከጮኸና አየሩን ሁሉ ከተቆጣጠረ በሁዋላ ውሃ የተቸለሰበት “ሕወሓት ብልፅግናን ለመቀላቀል በድርድር ላይ ነው” የሚለው የዋዜማ… Read more: “ትህነግ ብልፅግናን ለመቀላቀል በድርድር ላይ ነው ” የዜናው ሰም፣ ወርቅና የትህነግ ‘ ሃሰት ነው’ ማስተባበያ
- National Dialogue, Transitional Justice And Rehabilitation Process Pillars of Lasting Peace, Prosperity: CouncilThe Ethiopian National Security Council has issued a statement on latest developments in the country. In its… Read more: National Dialogue, Transitional Justice And Rehabilitation Process Pillars of Lasting Peace, Prosperity: Council
- ቀሲስ በላይ በተጠረጠሩበት ወንጀል ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀረቡ ዋስትና ተከለከሉየፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት አራዳ ምድብ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት የቀሲስ በላይ መኮንንን ጨምሮ የ3 ግለሰቦችን ጊዜ ቀጠሮ… Read more: ቀሲስ በላይ በተጠረጠሩበት ወንጀል ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀረቡ ዋስትና ተከለከሉ