በእንግሊዝ እየተካሄደ ያለው የቡድን 7 ሃገራት ስብስባ ዛሬ መግለጫ አውጥቷል:: በመግለጫው የኢትዮጵያ ጉዳይም ተካቷል:: በአንቀፅ 54 ላይ የሰፈረው መግለጭ ቃል በቃል የሚከተለውን ይላል።
ትርጉም
54. “በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ውስጥ እየተካሄደ ባለው ግጭት እና እየወጡ ባሉ ሪፖርቶች ምናልባት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በረሃብ ሁኔታ ውስጥ ሊሆኑ ስለሚችሉ የሰብአዊ አደጋዎች በጣም ያሳስበናል፡፡ የጾታ ጥቃትን ጨምሮ እየተፈፀሙ ያሉ አሰቃቂ ድርጊቶችን እናወግዛለን ፣ የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽን (OHCHR) ምርመራዎችንም በደስታ እንቀበላለን እንዲሁም በትግራይ ለተፈጸሙ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ሙሉ ተጠያቂነት እንዲሆኑና ወንጀለኞቹም ለህግ እንዲቀርቡ እንጠይቃለን፡፡ ግጭት በፍጥነት እንዲቆም ፣ ያልተዳረሰ ሰብዓዊ አቅርቦት ወደ ሁሉም አካባቢዎች እንዲደርስ እና የኤርትራ ኃይሎች በፍጥነት እንዲወጡ እንጠይቃለን፡፡ ለችግሩ ብቸኛ መፍትሄ ተአማኒ የፖለቲካ ሂደት ሁሉም ወገኖች እንዲከተሉ እንጠይቃለን፡፡ በቀጣይም የኢትዮጵያ መሪዎች የሰብአዊና የፖለቲካ መብቶችን በማክበር ላይ በመመስረት ብሄራዊ እርቅ እና መግባባት እንዲፈጠር ሰፋ ያለ ሁሉን አቀፍ የፖለቲካ ሂደት እንዲያራምዱ ጥሪ እናቀርባለን፡፡” ትርጉሙ የተወሰደው ከደጀኔ አሰፋ ነው።
በዚህ አንቀጽ መሰረት ኢትዮጵያ ያልተስማማቸው ከትህነግ ጋር ንግግር የሚባለውን ህሳብ ነው። አልተካተተም። ጥቅል የፖለቲካ ፈውስ እንደሚያስፈልግ መንግስትም አምኗል። አስቀድሞ ተናግሯል። የሚገባ ምክር ነው ተብሏል። አሜሪካ ያወጣቸው መግለጫ ሲጨመቅ አይነት ነውልል
- ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በከፍተኛ የውስጥ ችግር ውስጥ ናት፤ በጾሙ ማቅ ለብሰው በንስሃ ችግራቸውን ይፍቱየኢትዮጵያ ታሪክ ቁንጮ እንደሆነች የሚመሰከርላትና እጅግ ውብ ስብዕና ያላቸው አባቶች የሚጠቀሱላት ዕድሜ ጠገብቷ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በከፍተኛ የውስጥ ችግር… Read more: ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በከፍተኛ የውስጥ ችግር ውስጥ ናት፤ በጾሙ ማቅ ለብሰው በንስሃ ችግራቸውን ይፍቱ
- ሕብረቱ ከታገዱ የሩሲያ ንብረቶች የሚገኘውን ትርፍ ለዩክሬን ጦር መሳሪያ ግዢ ሊያውል ነውየአውሮፓ ሕብረት በአባል ሀገራቱ እንዳይንቀሳቀሱ ከታገዱ የሩሲያ ንብረቶች የሚገኘውን ትርፍ ዩክሬንን ጦር መሳሪያ ለማስታጠቅ ሊያውል መሆኑ ተሰምቷል፡፡ More stories… Read more: ሕብረቱ ከታገዱ የሩሲያ ንብረቶች የሚገኘውን ትርፍ ለዩክሬን ጦር መሳሪያ ግዢ ሊያውል ነው
- ሳኡዲ የምታስገነባው አዲስ ከተማ – “ኒዮም ሲቲ” (Neom City)በረሃን ወደ ከተማነት የመቀየር ጥበብ ልንለው እንችላለን፡፡ ከ1 ትሪሊየን ዶላር በላይ የሚፈጅ ውድ ሥራም ነው፡፡ ከገንዘቡ ባሻገር ብዙ እውቀቶች… Read more: ሳኡዲ የምታስገነባው አዲስ ከተማ – “ኒዮም ሲቲ” (Neom City)
- Ethiopia, Somalia dispute won’t transform into turmoil for the Horn of Africadeal between Ethiopia and Somaliland has sent waves of debates throughout the region, has even raised questions about the… Read more: Ethiopia, Somalia dispute won’t transform into turmoil for the Horn of Africa
- በአማራና ትግራይ ክልል ያሉ የወሰን ይገባኛል ጥያቄ በህዝብ ውሳኔ እንዲቋጭ ስምምነት ተደረሰትህነግ በበላይነት የሚመራው ኢህአዴግ ከፈርሰ በሁዋላ የተነሳውን ጦርነት ተከትሎ የአማራ ክልል ” ነጻ ወጡ” ባላቸው አካባቢዎች ለዓመታት የቆየ ውዝግብ… Read more: በአማራና ትግራይ ክልል ያሉ የወሰን ይገባኛል ጥያቄ በህዝብ ውሳኔ እንዲቋጭ ስምምነት ተደረሰ