የኮቪድ 19 ወረርሽኝ በሀገራት ኢኮኖሚ ላይ እያደረሰ ያለውን ጫና ለመቀነስ እና ወረርሽኙን ለመግታት እንዲሆን የአለም ባንክ በቅርቡ በተለይ ለታዳጊ ሀገራት የማገገሚያ ድጋፍ ማድረጉ አይዘነጋም።
ከዚህ ውስጥም ኢትዮጵያ ወደ 207 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ድጋፍ ከባንኩ አግኝታለች። ይህንን የአለም ባንክ የኮቪድ 19 ማገገሚያ የድጋፍ ገንዘብ ኢትዮጵያ ለክትባት ግዥ ልታውለው እንቅስቃሴ መጀመሯን ዋዜማ ከመንግስታዊ ምንጮች ስምታለች።
በዚህም መሰረት ጆንሰን ኤንድ ጆንሰን ከተሰኘው ከታዋቂው የአሜሪካ የመድሃኒት አምራች ኩባንያ የኮቪድ 19 ክትባት ለመግዛት ውል እንደፈፀመችም ተነግሯል።
ኢትዮጵያ የጆንሰን ኤንድ ጆንሰን የኮቪድ 19 ክትባትን ለመግዛት የፈፀመችው ውል 3 ሚሊየን ለሚጠጋ የክትባት ጠብታ (Dose) ሲሆን ከዚህ በተጨማሪም ወደ 4 ሚሊየን የሚጠጋ የአስትራ ዜኒካ ክትባትንም በግዥ ለማስገባት አስፈላጊው ሁሉ እንደተፈፀመ ከጤና ሚኒስቴር ምንጮች ስምተናል።
ኢትዮጵያ ኮቫክስ ከተሰኘው የኮቪድ 19 ክትባትን ለታዳጊ ሀገራት ለማዳረስ በተቋቋመው ጥምረት አማካኝነት በዚሁ አመት መጋቢት ወር ላይ ወደ 2 ነጥብ 2 ሚሊየን ጠብታ (Dose) የአስትራ ዜኒካ ክትባት ተረክባ የመጀመሪያ ዙር ክትባት ስታዳርስ መቆየቷ ይታወቃል።
ሁለተኛውን ዙር ክትባት ለማዳረስ የሚያስችል የአስትራ ዜኒካ ክትባት በተለይ 391 ሺህ የአስትራ ዜኒካ ክትባትን ሀገሪቱ በጥቂት ቀናት ውስጥ ከኮቫክስ ጥምረት ትረከባለች ተብሎም እየተጠበቀ ነው። ክትባቱ ምናልባትም በቀጣዮቹ አምስት ቀናት ኢትዮጵያ እንደሚገባም ይጠበቃል።
ከዚህ በተጨማሪም ከነሃሴ እስከ መስከረም ወር ድረስ 1 ነጥብ 7 ሚሊየን ጠብታ የአሰትራ ዜኒካ ክትባትን ለመረከብ እየተዘጋጀች የምትገኘው ኢትዮጵያ ሰሞኑን ከሚገባው ወደ 400 ሺህ ጠብታ ከሚጠጋው ክትባት ጋር በድምሩ ወደ 2 ነጥብ 2 ሚሊየን ጠብታ ክትባትን እንደምታገኝ ይጠበቃል።
ይህ ደግሞ በመጀመሪያው ዙር የአስተራ ዜኒካ ክትባት የከተበቻቸውን እና አዲስ የሚከተቡ ዜጎቿን በሙሉ ሁለተኛ ዙር የአስትራ ዜኒካ ክትባት ለማዳረስ እንደሚያስችላትም ዋዜማ ራዲዮ ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል።
- Kenya’s military chief dies in a helicopter crash, Nairobi declares three days of national mourningKenya’s military chief Gen. Francis Ogolla died in a helicopter crash west of the country, President William Ruto… Read more: Kenya’s military chief dies in a helicopter crash, Nairobi declares three days of national mourning
- U.S. stops UN from recognizing a Palestinian state through membershipCGTN – The United States on Thursday stopped the UN from recognizing a Palestinian state by casting a… Read more: U.S. stops UN from recognizing a Palestinian state through membership
- Israel launches missile attacks on Iran: reportCGTN – Israeli missiles have hit a site in Iran, ABC News reported late on Thursday, citing a… Read more: Israel launches missile attacks on Iran: report
- ዓለም ባንክና መንግስት በአሜሪካ እየመከሩ ነው፤ ኢትዮጵያ ” የብርን የምንዛሬ አቅም ቀንሱ” ጥያቄ አልተቀበለችምዓለም ባንክና የዓለም ዓቀፉ የገንዘብ ተቋም ኢትዮጵያ የጠቀችውን ብድር ለመፍቀድ ያቀረቡት ዋና ቅድመ ሁኔታ የብርን የመግዛት አቅም ዝቅ… Read more: ዓለም ባንክና መንግስት በአሜሪካ እየመከሩ ነው፤ ኢትዮጵያ ” የብርን የምንዛሬ አቅም ቀንሱ” ጥያቄ አልተቀበለችም
- ቀሲስ በላይ ከ 6.5 ሚሊዮን ዶላር በላይ ህገወጥ የገንዘብ ዝውውር ወንጀል ታስረው ፍርድ ቤት ቀረቡMore stories ኢትዮጵያን የምናፈርስበት “ዓመት፣ ወር፣ ቀን እና ሰዓት አሁን ነው” – ትህነግSeptember 26, 2021 አማራ ክልል ባልታወቁ… Read more: ቀሲስ በላይ ከ 6.5 ሚሊዮን ዶላር በላይ ህገወጥ የገንዘብ ዝውውር ወንጀል ታስረው ፍርድ ቤት ቀረቡ