በፎቶው ላይ የሚታዩት የውሃ፣ መስኖ እና ኢንርጂ ሚንስትሩ ስለሺ በቀለ (ዶ/ር፣ ኢንጂነር፣ የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር ሊያ ታደሰ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ፣የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት፣የትራንስፖርት ሚንስትሯ ዳግማዊት ሞገስ፣ዛዲግ አብርሀ፣ የብሔራዊ ባንክ ገዢው ዶ/ር ይናገር ደሴ፣ ፕ/ር ሂሩት ወ/ማርያም፣ የአገር አቀፍ ምዘና እና ፈተናዎች ኤጀንሲ ዳይሬክተር ዲላሞ ኦቶሬ ናቸው።
በዘንድሮው ምርጫ ብልፅግና ፓርቲ ከ436 መቀመጫዎች ውስጥ 410 ያሸነፈ ሲሆን ለቀጣዩ አምስት አመታትም መንግሥት መመስረት የሚያስችለውን ወንበር አግኝቷል።
ለዘመናት የአገሪቱ ዋነኛ የፖለቲካ ማዕከል ሆና በቆየችው አዲስ አበባ በርካታ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ከተማዋ ላይ ባተኮረ መልኩ ፖሊሲዎችን ሲቀርፁና ሲንቀሳቀሱ ይታያሉ።
በዘንድሮው ምርጫ ብዙ ትኩረት በነበረባት አዲስ አበባ የተመዘገቡ መራጮች ቁጥር 1,819,343 ሲሆን ከዚህም ውስጥ 99ኛው በመቶ ድምፅ ሰጥቷል።
አዲስ አበባ ከተማ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 23 መቀመጫዎች ያሏት ሲሆን ገዢው ፓርቲ ብልፅግና 22 መቀመጫዎችን ሲያሸንፍ በግል የተወዳደሩትና የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት መቀመጫ አግኝተዋል።
ለመሆኑ በቀጣዮቹ አምስት አመታት አዲስ አበባን በፓርላማ የሚወክሏት እነማን ናቸው?
- ምርጫ ክልል 1- ፕ/ር ኢያሱ ኤልያስ
- ምርጫ ክልል 2 ብርሃነ መስቀል ጠና
- ምርጫ ክልል 3 የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር ሊያ ታደሰ
- ምርጫ ክልል 4 ሙሉ ይርጋ
- ምርጫ ክልል 5 ያስሚ ወህቢ
- ምርጫ ክልል 6 ዶክተር ወንድሙ ተክሌ
- ምርጫ ክልል 7 በሕዳሴ ግድብ ዙሪያ የኢትዮጵያ አቋም ለአረቡ ዓለም በማንጸባረቅ የሚታወቁት መሐመድ ከማል አሊ አል-አሩሲ
- ምርጫ ክልል 8 የትራንስፖርት ሚንስትሯ ዳግማዊት ሞገስ
- ምርጫ ክልል 10 ዶ/ር ቤተልሄም ላቀው
- ምርጫ ክልል 11 ፕ/ር ሂሩት ወ/ማርያም፣
- ምርጫ ክልል 12 እና 13 ዕጩ ሲሆኑ ዶ/ር ስንታየሁ ወ/ሚካኤል
- ምርጫ ክልል 15 ህይወት ሞሲሳ
- ምርጫ ክልል 16 ሰሃርላ አብዱላሂ
- ምርጫ ክልል 17 የውሃ፣ መስኖ እና ኢንርጂ ሚንስትሩ ስለሺ በቀለ (ዶ/ር፣ ኢንጂነር)፣
- ምርጫ ክልል 18 ዛዲግ አብርሀ
- ምርጫ ክልል 19 ዶ/ር ትዕግስት ውሂብ
- ምርጫ ክልል 20 የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ
- ምርጫ ክልል 21 እና 22 የብሔራዊ ባንክ ገዢው ዶ/ር ይናገር ደሴ
- ምርጫ ክልል 23 የአገር አቀፍ ምዘና እና ፈተናዎች ኤጀንሲ ዳይሬክተር ዲላሞ ኦቶሬ
- ምርጫ ክልል 24 ዶ/ር ከይረዲን ተዘራ
- ምርጫ ክልል 25 ዶ/ር ቶፊቅ አብዱላሂ
- ምርጫ ክልል 26 እንዳልካቸው ሌሊሳ
- ምርጫ ክልል 28 በግል ተወዳዳሪነት የቀረቡትና የጠቅላይ ሚኒሰትሩ አማካሪ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ናቸው።
የክልል ምክር ቤቶችን በምንመለከትበት ወቅት ብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባን ምክር ቤት ሁሉንም 138 መቀመጫዎችን አሸንፏል።
ምርጫ 2013 በጨረፍታ
- 37,408,600 መራጮች ተመዝግበዋል ከዚህ ውስጥ 20,317,472 ወንዶችና 17, 091, 128 ሴቶች ናቸው
- 47 ፓርቲዎች 8,209 እጩዎችን አቅርበዋል 125 የግል ተወዳዳሪዎችም
- 634 የምርጫ ክልሎችና 49, 407 የምርጫ ጣቢያዎች
- 52,700 የምርጫ አስፈጻሚዎች፤ በእያንዳንዱ የምርጫ ጣቢያ 5 አስፈጻሚና 1 የኮቪድ-19 ቁጥጥር ባለሙያ
- ሰኔ 14/2013 ዓ.ም በተደረገው ምርጫ ለ445 የፓርላማ መቀመጫዎች ድምጽ ተሰጥቷል
- ጳጉሜ 01/2013 ደግሞ ለቀሪዎቹ 64 ወንበሮች ድምጽ ይሰጣል
ምስጋና ፎቶና ዘገባ ቢቢሲ
- Somaliland offended by G7 referring the Republic of Somaliland as “Somaliland Region of Somalia” The Republic of Somaliland, is a sovereign state with its own laws and constitution, reaffirmed by the people of… Read more: Somaliland offended by G7 referring the Republic of Somaliland as “Somaliland Region of Somalia”
- ” በትጥቅ ትግል ውስጥ ያሉ ወገኖቻችን አሁንም ሳይመሽ ቶሎ ወደ ድርድሩ እንዲገቡ በትህትና እንጠይቃለን ” ፕ/ር መስፍን አርአያየኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በሌላ መንገድ እየታገሉ ይገኛሉ ያላቸው አካላት ወደ ምክክር መድረኩ እንዲገቡ ጥሪ አቀረበ። ኮሚሽኑ ከዚህ ቀደም… Read more: ” በትጥቅ ትግል ውስጥ ያሉ ወገኖቻችን አሁንም ሳይመሽ ቶሎ ወደ ድርድሩ እንዲገቡ በትህትና እንጠይቃለን ” ፕ/ር መስፍን አርአያ
- የቡድን ሰባት አገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በኢትዮጵያ ጉዳይ የይሁንታና የስጋት ቅልቅል መግለጫ ሰጡየቡድን ሰባት ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በተለያዩ ጉዳዮች ላይ መግለጫ ሲሰጡ እግረመንገዳቸውን ኢትዮጵያን አስመልክቶ በበጎ ጎኑንና በስጋት ከፍለው መግለቻቸው… Read more: የቡድን ሰባት አገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በኢትዮጵያ ጉዳይ የይሁንታና የስጋት ቅልቅል መግለጫ ሰጡ
- Foreign firms’ local market involvement entails economic dynamismPermitting foreign firm’s involvement in the import, wholesale and retail business, which was restricted to local companies, would bring… Read more: Foreign firms’ local market involvement entails economic dynamism
- መንግስት የፕሪቶሪያው ስምምነት መጣስና የአማራን፣ትግራይና አፋር ህዝብን ማህበራዊ ዕረፍት መንሳት ተቀባይነት የለውም ሲል አስጠነቀቀMore stories ከምርጫው ራሳቸውን እንደማያገሉ ፓርቲዎች አስታወቁ፤ “ይህ ማለት ግን ቢሸነፉ ለአሸናፊው እውቅና መስጠት አይደለም”June 13, 2021 መንግስት “በመላው… Read more: መንግስት የፕሪቶሪያው ስምምነት መጣስና የአማራን፣ትግራይና አፋር ህዝብን ማህበራዊ ዕረፍት መንሳት ተቀባይነት የለውም ሲል አስጠነቀቀ