አሸባሪው ህወሃት ለትግራይ ክልል የሚላከው የሰብዓዊ ድጋፍ እንዳይጓጓዝ ማስተጓጎሉና ስላሳ የሚጠጉ እህልና ቁሳቁስ የጫኑ ተሸከርካሪዎች እንዳያልፉ ከባድ መሳሪያ በመተኮስ መንገስድ መዝጋቱ ተገለጸ። መንግስት በአፋር በኩል የትህነግ ሃይል ድንበር አልፎ ሲመጣ ለምን ዝምታን እንደመረጠ አልተገለጸም። ይሁንና ክልሉ የጸጥታ ሃይሉና ሕዝቡ እንዲዘጋጅ አሳስቧል።
ኢዜአ እንዳለው ለትግራይ ክልል የሚላከው የሰብዓዊ ድጋፍ በአፋር በኩል ወደ መቀሌ ሲጓጓዝ የአሸባሪው የህወሃት ቡድን አካባቢውን በከባድ መሳሪያ በመደብደብ መንገድ ዘግቷል። መንግስት ወደ ትግራይ ክልል ሰብዓዊ ድጋፍ በተገቢው መልኩ ለማዳረስ የተናጥል ተኩስ ማቆሙ ተከትሎ ወደ አጥቂነት የተዛወረው አሸባሪው ቡድን ይህን ተግባሩን እንዲያቆም የገሰጸው አካል እንደሌለ መንግስት በተደጋጋሚ እያስታወቀ ነው።
ለትግራይ ክልል ሰብዓዊ ድጋፍ እየቀረበ መሆኑን የብሔራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን በይፋ ባስታወቀበትና ተጨማሪ የኬላ ጣቢያዎችን በማቋቋም ፍተሻውን በማጣደፍ እርዳታ ቶሎ ቶሎ ወደ ተረጂዎች እንዲደርስ እየሰራ መሆኑንን ባመለከተበት ወቅት አሸባሪው ሃይል አፋርን በከባድ መሳሪያ የሚደበድብበት ምክንያት ግልጽ አይደለም። ይሁን እንጂ አቶ ጌታቸው በጤና ሆነው ከሚናገሩት አግባብ ውጭ አንደበታቸው እየተጎተተ ለቪኦኤ ” በወልቃይት በኩል እርዳታ እንዲገባ እናደርጋለን” ካሉት ጋር ሊገናኝ እንደሚችል ግምት አለ።
ዛሬ በአፋር ክልል በኩል ምግብና ምግብ ነክ ያልሆኑ ድጋፎችን የጫኑ 60 ተሽከርካሪዎች ወደ ትግራይ ክልል እየተጓዙ ሳለ የአሸባሪው ህወሃት ቡድን ተኩስ በመክፈት እንዳይጓጓዝ መንገድ መዝጋቱ ኢዜአ ሲዘግብ መንገዱ እንዲከፈት ምን ጥረት እንደተደረገ የትኛውንም ወገን ጥቀሶ ያለው ነገር የለም።
ለትግራይ ክልል የሚሂድ የእርዳታ ቁስና ምግብ ነክ የሆነ ተፍትሾ እንዲያልፍ ሰርዶ 60 እና ሚሌ ኬላዎች ላይ እየተሰራ ቢሆንም፤ አሸባሪው ህወሃት በዞን አራት ያሉ የአፋር ፖሊስና ልዮ ሀይል አባላትና ማህበረሰብን በከባድ መሳሪያ እየደበደበ “ወደ ትግራይ የሚሄድ እርዳታ አይኖርም” በማለት ሰርዶ ኬላ ላይ መዝጋቱን ከአካባቢ የተገኙ ምንጮች ለኢዜአ ተናግረዋል።
ህወሃት የተኩስ አቁም ውሳኔውን “አልቀበልም” በማለት ግጭቱን ወደ አፋር ክልል ለማስፋት እየሰራ መሆኑም ታውቋል። በቅርቡም መንግስት ሁኔታዎች በማመቻቸቱ ለክልሉ ሰብዓዊ ድጋፍ የጫኑ 61 ከባድ ተሽከርካሪዎች ትግራይ ክልል መድረሳቸው ይታወሳል።
ከዚህ ውስጥ 34ቱ ምግብ ነክ ድጋፎችን የጫኑ ሲሆን፤ 26 ተሽከርካሪዎች ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁሶችን የጫኑ ሲሆኑ፤ ከ47 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ የጫነ አንድ ከባድ ተሽከርካሪም መቀሌ መድረሱ ተዘግቧል።
በአፋር ክልል ያለውን መንገድ ማስተጓጎል የተፈለገው በውልቃይት በኩል ድንበሩ እንዲከፈት ያለውን ግፊት ለመጨመር ሆን ተብሎ የተደረገ እንደሆነ የሚገልጹ አሉ። ትህነግ በወልቃይት በኩል ያለውም ግምብ ማለፍ ስለማይቻለው በአፋር በኩል ችግር በመፍጠር በወዳጆቹ አገራት አማካይነት የሱዳን ድንበር እንዲከፈትለት ተጨማሪ ጫና ይፈጥራል ተብሎ ይገመታል። በሌላ በኩል ከመንግስት በኩል ከወታደራዊ ጠቀሜታ አንጻር አሸባሪ ቡድኑ ወደ አፋር ሜዳማ ቦታ እንዲወጣ ይፈለጋል የሚሉም አሉ። እነዚህ ክፍሎች አክለው እንደሚገልጹት ሳይሆን ይህ ሃይል አፋርን ወሮ የጅቡቲን መንገድ ለማስተጓጎል ህልም እንዳለው፣ ወደ አሰብም የማምራት እቅድ እንዳለው ለወዳጆቹ መረጃ መስተቱን የሚያውቁ እየተናገሩ ነው።
- Somaliland offended by G7 referring the Republic of Somaliland as “Somaliland Region of Somalia” The Republic of Somaliland, is a sovereign state with its own laws and constitution, reaffirmed by the people of Somaliland in a… Read more: Somaliland offended by G7 referring the Republic of Somaliland as “Somaliland Region of Somalia”
- ” በትጥቅ ትግል ውስጥ ያሉ ወገኖቻችን አሁንም ሳይመሽ ቶሎ ወደ ድርድሩ እንዲገቡ በትህትና እንጠይቃለን ” ፕ/ር መስፍን አርአያየኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በሌላ መንገድ እየታገሉ ይገኛሉ ያላቸው አካላት ወደ ምክክር መድረኩ እንዲገቡ ጥሪ አቀረበ። ኮሚሽኑ ከዚህ ቀደም ተደጋጋሚ ጥሪ ማቅረቡ… Read more: ” በትጥቅ ትግል ውስጥ ያሉ ወገኖቻችን አሁንም ሳይመሽ ቶሎ ወደ ድርድሩ እንዲገቡ በትህትና እንጠይቃለን ” ፕ/ር መስፍን አርአያ
- የቡድን ሰባት አገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በኢትዮጵያ ጉዳይ የይሁንታና የስጋት ቅልቅል መግለጫ ሰጡየቡድን ሰባት ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በተለያዩ ጉዳዮች ላይ መግለጫ ሲሰጡ እግረመንገዳቸውን ኢትዮጵያን አስመልክቶ በበጎ ጎኑንና በስጋት ከፍለው መግለቻቸው ላይ አክለዋል። በኢትዮጵያ… Read more: የቡድን ሰባት አገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በኢትዮጵያ ጉዳይ የይሁንታና የስጋት ቅልቅል መግለጫ ሰጡ
- Foreign firms’ local market involvement entails economic dynamismPermitting foreign firm’s involvement in the import, wholesale and retail business, which was restricted to local companies, would bring a new dynamism… Read more: Foreign firms’ local market involvement entails economic dynamism
- መንግስት የፕሪቶሪያው ስምምነት መጣስና የአማራን፣ትግራይና አፋር ህዝብን ማህበራዊ ዕረፍት መንሳት ተቀባይነት የለውም ሲል አስጠነቀቀMore stories ከንቲባ አዳነች የአዲስ አበባን ጉድ ለሚመሩት ሕዝብ ይፋ አደረጉ፤ ሪፖርቱን በርካቶች ከሳቸው ሲጠብቁት ነበርJanuary 26, 2021 ምንም ይሁን ምን ኢትዮጵያ… Read more: መንግስት የፕሪቶሪያው ስምምነት መጣስና የአማራን፣ትግራይና አፋር ህዝብን ማህበራዊ ዕረፍት መንሳት ተቀባይነት የለውም ሲል አስጠነቀቀ