በኢትዮጵያ መፈንቅለ መንግስት ከተደረገ በሁዋላ እነማን ባለ ስልጣን ሆነው እንደሚመደቡ የሚያሳይ ሰነድ መያዙ ተሰማ። ሰነዱ የተያዘው ፖሊስ በተመረጡ ድንገተኛ ቦታዎች ባካሄደው ፍተሻ እንደሆነ ታውቋል። መከላከያን ለማፍረስ የሚደረግ ዝግጅት አስመልክቶ ውይይት መደረጉን የሚያሳይ መረጃም ተገኝቷል።
በትናንትናው ዕለት ፖሊስ የአሸባሪው ትህነግ ደጋፊ ናቸው ያላቸውን ክፍሎችና ንግድ ቤቶች በድንገትና በጥቆማ ፈትሾ በርካታ ቁሳቁሶችን፣ መሳሪያዎችን፣ የወታደራዊ ማዕረግ፣ ሃሺሽ፣በርካታ የውጭ ምንዛሬ፣ የጦር መሳሪያ፣ የጦር መሳሪያ መነጽሮች፣ የስዳተላይት መገናኛና ከአሸባሪው ሃይል ጋር የተካሄዱ ውይይቶች እንዲሁም ሰነዶች እንዳገኝ ማስታወቁ አይዘነጋም።
የኢትዮ12 የአዲስ አበባ ተባባሪ ያነጋገራቸውን ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ አካሎች ጠቅሶ እንዳለው “ሰነድና የድምጽ ማስረጃ” ሲሉ የፊደራል ፖሊስ ከተቀሰው ውስጥ የምንግስት ግልበጣ ከተካሄደ በሁዋላ ትህነግ እንዲሾሙ ያግባባቸውና ሴራው ውስጥ ያሉ አካላት ስም ዝርዝርና ሹመታቸው ተገኝቷል።
“የተቃዋሚ ፓርቲ አመራር ነን” የሚሉና የሽግግር መንግስት ካልተቋቋመ በሚል አጥብቀው ሲከራከሩ የነበሩ ቁንጮዎች በሹመት ዝርዝር ውስጥ እንዳሉበት ተመልክቷል። ለጊዜው ለምረመራ ስራ ሲባል ስም ዝርዝር መጥቀስ አግባብ እንዳልሆነም ተባባሪያችን አስታውቋል።
የሽብር ቡድኑ አመራሮችና ደጋፊዎች የኢትዮጵያን መከላከያ ሰራዊት ” የአብይ ጦር” እያሉ ደጋግመው የሚጠሩት በምክንያት እንደሆነ ያመለከተው ተባባሪያችን ባገነው መረጃ ከተገኘው የውይይት ሰነድ ውስጥ የአገር መከላከያ እንደሚፈርስ የተደረገ ውይይት ይገኝበታል።
ሟቹ ሴኮ ቱሬ ሰራዊቱን ” ከጥቅም ውጭ አድርገነዋል” ማለቱን ያስታወሱት የዜናው ባለቤቶች ” መንግስት ሆነው ጎን ለጎን የራሳቸውን ሃይል ካደራጁ በሁዋላ አስቀድሞ መከላከያውን ማፍረስና መምታት የተፈለገው ለውጭ ሃይሎቹ ድጋፍ ሲባል ነበር” ብለዋል። ሲያስረዱም “የአገር መከላከያ ፈራርሷል በሚል የባለ ተጋ ዓገሮችን ጥቅም ማስከበር የሚችሉት እነሱ ብቻ እንደሆኑ አድርጎ ለማሳየት ያቀዱት እቅድ ነው”
አሁን ተገኘ በተባለው የውይይት ሰነድ የአገር መከላከያ ፈርሶ ትግራይ የተደራጀው ሃይልና ከኦነግ ሸኔ በሚመጣ መጠነኛ ሃይል መልሶ ለማደራጅት እቅድ መኖሩን አመላካች ሆኖ ተገኝቷል።
በተደጋጋሚ የአገር መከላከያን ስም ለማቆሸሽ የሚደረገው ዘመቻ ተራ ዘመቻ ሳይሆን ጦሩን ልክ እንደ ቀድሞ በትኖ ለማኝ ለማድረግ ይረዳ ዘነድ ቅድመ ዝግጅት መሆኑንን ተባባሪያችን ዜናውን የነገሩትን ጠቅሶ አመልክቷል።
የአሸባሪው ቡድን ደጋፊዎች በገሃድ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊትን የሚያራክስና ጸረ ሕዝብ አቋም እንዳለው መቀስቀስ ከጀመሩ መሰንበታቸው፣ በሃያ ዓመት የትግራይ ቆይታው ህዝብ አክባሪ፣ ታማኝ፣ የልማት አጋር፣ በተለይ የትግራይ ህዝብን ሰላም ሲተብቅ የኖረ፣ ዕድሜውን በምሽግ ውስጥ ያሳለፈ ሰራዊት ሆኖ ሳለ ሳያስበው በተኛበት ታርዶ፣ ተረሽኖ፣ እንደ ምርኮኛ ታግቶ፣ አስከሬኑ አሞራ እንዲበላው ተደርጎ፣ የሴቶች ጡታቸው ተቆርጦ … በታሪክ ሊሽር የማይችል ግፍ እንደተፈጸመበት ምስክሮች በተደጋጋሚ መናገራቸው የሚዘነጋ አይደለም። ይህ የሆነው ብሄር ተመርጦ ሳይሆን በኦሮሞ፣ በአማራ፣ በሶማሌ፣ በጋምቤላ፣ በደቡብ… ከትግራይ በቀር በሁሉም ብሄረሰብ አባላት ላይ እንደሆነም አስታውቀው ነበር።
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ትጥቅ እንዲፈቱ ከተደረጉ በሁዋላ ጡታቸው ስለተቆረጠ፣ እንግልትና ስቃይ ስለደረሰባቸው፣ ሲኖ ትራክ ስለተነዳባቸው፣ ተገደው ስለተደፈሩ የመከላከያ ሴት አባላት እስካሁን ያለው ነገር የለም። ኮሚሽኑ እነ አቶ ስብሃትን እስር ቤት እየተመላለሰ እንደሚተይቅ ገልጾ ሪፖርት ሲያወጣ ግፍ የተፈጸመባቸው ሴት ወታደሮች አዲስ አበባ ማገገሚያ እያሉ እንዲያናግራቸው ቢጠይቁም ፈቃደኛ አልሆነም። ከቀናት በፊት የትግራይ ልጆች በጅምላ እየታሰሩ መሆኑንን ተቃውሞ ሪፖርት ሲያዘጋጅ ፖሊስ በይፋ ያሳየውን ኢግዚቢት በሪፖርቱ አላካተተም። ኮሚሽኑ የማይካድራን ጭፍጨፋ የመጨረሻ ሪፖርትም እስካሁን ይፋ አላደረገም።
ገለልተኛ ዜጎችና ነዋሪዎች ንጽህ የትግራይ ተውላጆች እንግልት እንዳይደርስባቸው፣ ፖሊስ አስፈላጊውን ሁሉ ጥንቃቄ ሊያደርግ እንደሚገባ በማህበራዊ ገጻቸው ሲያሳብቡ ማስተዋል ተችሏል።
- የባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ ለኢንቨስተሮች መሰጠቱን የተቃወሙ ሦስት ምሁራን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ደብዳቤ ጻፉ“እሳቸው ይሄንን ነገር ሰምተውታል ብዬ አላስብም። ከሰሙ እንደሚያስቆሙት እርግጠኛ ነኝ” ከአምስት አስርት ዓመታት በላይ ያስቆጠረው የባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ ከፊል ስፍራ ተቆርሶ ለግብርና ኢንቨስተሮች መሰጠቱ ያስቆጣቸው ሦስት ምሁራን ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ደብዳቤ ጻፉ። የባቢሌ ፓርክ ደን ተመንጥሮ ለኢንቨስተሮች መሰጠቱ ከፍተኛ የድርቅ አደጋ እንደሚጋርጥ በመግለጽም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጣልቃ እንዲገቡ ምሁራኑ በደብዳቤያቸው … Read moreContinue Reading
- የበርሊን ማራቶን ባለማዕረግ ትግስት እነ ዱቤ ጂሎ ቢሳተፉ ታዝረከርካቸው ነበርበማራቶን ከሁለት ደቂቃ በላይ ማሻሻል እጅግ የሚደነቅና ያልተለመደ ነው። ባለሙያዎቹ ወይም አሰልጣኞቹ የሮጠችበትን ፍጥነት በሰዓትና ርቀት ከፋፍለው ቢያቀርቡት ምን አልባትም ወንዶችን የሚገዳደር ፍጥነት ተጠቅማ ሮጣለች። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ተቴክኒክ ዳይሬክተርና የአትሌቶች ኮሚሽን ሰብሳቢ የነበሩት የዛሬው የተከበሩ ዱቤ ጅሎ አይነቱን ሯጮችን አዝረክርኮ ማሸነፍ የሚያስችላትን ሃይል አሳይታለች። የበርሊና ባለ ማዕረግ ትዕግስት!! ተግስት … Read moreContinue Reading
- የባህር ዳር ነዋሪዎች- ኢትዮጵያን ዜጎች በሁሉም ቦታ እኩል የሚስተናገዱባት ሀገር ማድረግ ይገባልየባህር ዳር ነዋሪዎች የሕዝብን ጥያቄ የመፍታት አቅም፣ ፍላጎት እና ቅንነት ያለው አመራር በመፍጠር ሕዝብን መካስ እንደሚያስፈልግ፣ ኢትዮጵያ በዘር ከመገፋፋት እና ከመጠቃቃት ነጻ የኾነች ፣ዜጎች በሁሉም ቦታ እኩል የሚስተናገዱባት ሀገር እንድትኾን ማድረግና የፌዴራል መንግሥት የአማራ ሕዝብ ኅብረ ብሔራዊ እና ልማት ወዳድ እንጅ ጦርነትን የማይፈልግ መኾኑን በውል በመገንዘብ የሕዝቡን ተዘዋውሮ የመሥራት እና … Read moreContinue Reading
- ለወልቃይት ጠገዴ ሴቲት ሁመራ አንድ ሚሊዮን የጉልበት ሰራተኛ ይፈለጋል፤ ከአንድ ነጥን አንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ሰሊጥ ይጠበቃል“ከየትኛውም የኢትዮጵያ ክልል አስተማማኝ ሰላም ያለው እዚህ ነው። ለሰራተኞች እንደ ቤተሰብ ዝግጅት አድርገናል። ኑ” ሲሉ የተሰሙት አምስት መቶና ሶስት መቶ ሄክታር ሰሊጥና ማሽላ ያመረቱ ባለሃብቶች ናቸው። የዞኑ ግብርና ቢሮ ሃላፊ እንዳሉት አንድ ሚሊዮን አንድ መቶ ሃምሳ ሁለት ሺህ ኩንታል የሰሊጥ ምርት ስለሚጠበቅ ከአንድ ሚሊዮን በላይ የሰራተኛ ሃይል ያስፈልጋል። የዞኑ አርባ … Read moreContinue Reading
- የጎንደርን ከተማ ምን አይነት ተኩስ እንደሌለ ተገለጸ፤ ጎንደር ተይዛለች ተብሎ ነበር“ጎንደር ከተማን ሙሉ በሙሉ ይዘናታል” ሲሉ ስማቸው እንዳይገለጽ ጠይቀው ለጀርመን ድምጽ መረጃ በሰጡ የአማራ ሕዝባዊ ኃይል ፋኖ ቃል አቀባይ አየር ማረፊያውን ሆን ብለው እንዳልያዙ አመልክተዋል። እሳቸው ተናገሩ የተባለው በጀርመን ድምጽ እየተሰማ በለበት ሰዓት በተመሳሳይ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ውጊያ መደረጉን ሳያስተባብል ከተማዋን ለመያዝ የገባው ሃይል መደምሰሱን አሃዝ ጠቅሶ አመልክቷል። አገር መከላከያም … Read moreContinue Reading