Invading #Afar and killing Afars will only make Afars stronger but will freeze the relations between brotherly people of Afar and Tigray. As your lies fades away the truth is coming forward. We know the truth and you're responsible! 3/3.@UNICEF @PowerUSAID@SecBlinken @WFP pic.twitter.com/nH86NwCRvE
— Kontie Moussa_ኮንቴ ሙሳ (@kontiem) August 11, 2021“አፋርን መውረርና የአፋርን ህዝብ መጨፍጨፍ ጠንካራ ያደርገናል። በሌላ በኩል ደግሞ በአፋርና በትግራይ ክልል ሕዝብ መካከል ያለውን ግንኙነት ይገለዋል። ቅጥፈታችሁ እየወየበና እየደበዘዘ፣ እውነት ወደ አደባባይ እየመጣች ነው። እውነቱን እናውቀዋለን። ተጠያቂዎቹ እናንተ ናቹህ” ሲሉ አምርረው ያስታወቁት ዶ/ር ኮንቴ ሙሳ ናቸው።
ዶክተር ኮንቴ ይህን ያሉት ጌታቸው ረዳ ” ከደሙ ንጹህ ነን” በሚል ጭፍጨፋውን አሸባሪው ትህነግ ሳይሆን መንግስት እንድፈጸመው ጥቅሰው በቲወተር ገጹ ላሰራጨው ሲመልሱ ነው።
ዶ/ር ኮንቴ ጭፍጨፋው ሲፈጸም ጋሊኮማ ላይ የትህነግ ሃይል ማሳከር ሲፈጽም በስፍራው የመንግስት ሰራዊት እንዳልነበር አስታውቀዋል። በትናንትናው ዕለት ስምንት የቤተሰብ አባላት በሚዘገንን ሁኔታ መጨፍጨፋቸውን ይፋ ባደረጉበት የቲውተር አውዳቸው ላይ እንዳስታወቁት የዩኒሴፍን ተዓማኝነት ሁሉ ጥርጣሬ ውስጥ እንደሚያስገቡ አመላክተዋል።
የተደረገውን ተኩስ አቁም ተከትሎ ለምን ጉዳይ አፋርን እንደወረረና፣ በምን ምክንያት 240 ንጹሃንን ከተጠለሉበት ድረስ ዘልቆ ለመጨፍጨፍ እንደወሰነ ትህነግ እስካሁን በገሃድ በዝርዝር ያለው ነገር የለም። ይሁን እንጂ ዶክተር ኮንቴ እንዳሉት በስፍራው ያልነበረውን የመከላከያ ሃይል አውግዞ አጭር የቲውተር ሃሳብ ለጥፏል።
አንድ መቶ ሰባት ህጻናት የተጨፈጨፉበት ትዕንት ቆስለው ህክምና በማድረግ ላይ ብሚገኙ አካላት ምስክርነት እየተሰጠበት ቢሆንም የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን እስካሁን ምንም አስተያየት አልሰጠበትም።
ትግራይን ሄዶ የማየት እድል ያልነበረው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ከማንና እንዴት እንደሚያገኘው ግልጽ ሳይሆን ተከታታይ መረጃ ሲያከታትል እንዳልነበረ፣ ዛሬ በአፋር ሆስፒታል ያሉ እማኞችን ሄዶ ለማነጋገር ይህን ያህል ጊዜ መውሰዱ የዶክተር ዳንዔልን አቋም ይበልጥ ጥያቄ ውስጥ አስገብቷል።
ከስፍራው የሚወጡ መረጃዎች ትህነግ ጭፍሮቹን አሰማርቶ አስገድዶ መድፈር ፈጽሟል። ሕጻናትን ጭፍጭፏል። ዝርፊያ አካሂዷል። ከፍተኛ የተባለ የሰብአዊ መብት ጥሰት ፈጽሟል።
ዛሬ ረፋዱ ላይ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ወደ ስፍራው ቡድን መላኩን አውስቶ፣ ስጋት እንደገባው ጠቁሞ አጭር ጥሪ አሰምቷል። ድርጅቱ ትህነግ በወረራቸው አካባቢዎች ስለተፈናቀሉ፣ ስለተገደሉና ስለተዘረፉ ሰዎች እስካሁን ያለው ነገር የለም። ከንግሊዝ ተመልሰው ድርጅቱን የሚመሩት ዶ/ር ዳንኤል የማይካድራውን ጭፍጨፋ ሪፖርት ከዳፈኑ በሁዋላ በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገር ተዓማኝነታቸው እየወረደ እንደሚገኝ በርካቶች እያወሱ ነው።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የአፋር ክልል መንግስት በግፍ ለተጨፈጨፉት ወገኖች የሶስት ቀን ሃዘን አውጇል። ባንዲራ ዝቅ ብሎ እንዲውለበለብ አድርጓል።
ዶክተር ኮንቴ የተቃዋሚ ፖለቲካ አመራር፣ ኢትዮጵያዊ አቋማቸው ላይ መዛነፍ የሌላቸው፣ ህዝብ የሚወዳቸው ፖለቲከኛ ናቸው።
በአፋር ንጹሃን ላይ ጭፍጨፋ በተፈጸመ ማግስት መንግስት የዜጎቹን ሰላም ለማስጠበቅ ሲል በይፋ የማጥቃት እርምጃ እንዲወሰድ መመሪያ እንደሚሰጥ አስቀድመው የገለጹ የአሜሪካ ባለስልጣናት ነበሩ።
- አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎችባንኩ የክፍያ ሰነድ ቀረበለት። ማጣሪያ ጥያቄ ለህብረቱ አቀረበ። ሃሰት ሆኖ ተገኘና ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን ያዘ። ጉዳዩ ወደ ህግ አመራ። አሁን ምኑ ነው አፍሪካ ህብረትን ስጋት ላይ ጥሎት አካውንቱን… Read more: አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎች
- የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል 300 ቢሊዮን ብር የንግድ ባንክ ዕዳ አለብኝ አለ፤ ዕዳውና የክፍያው ጫና እንደከበደውም አስታውቋልየኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከንግድ ባንክ 300 ቢሊዮን ብር ዕዳ እንዳለበት ተገለጸ። የዕዳ ጫናውን ለማቃለል የባንክ ወልዱም ጭምር ተፅእኖ እያሳደረ መሆኑም ተመልክቷል። የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል የዕዳ ጫናን ለማቃለል… Read more: የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል 300 ቢሊዮን ብር የንግድ ባንክ ዕዳ አለብኝ አለ፤ ዕዳውና የክፍያው ጫና እንደከበደውም አስታውቋል
- ዋና ዋና የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ይዘቶች – ሲጨመቁመግቢያ ሽግግር ፍትህ ጉልህ የመብት ጥሰቶች በተፈፀመባቸው ሀገራት ተጠያቂነትን ለማስፈን እና ተበዳዮችን ለመካስ ጥቅም ላይ ሲውል ቆይቷል፡፡ በሀገራችንም የሽግግር ፍትህ አስፈላጊነት ታምኖበት ፖሊሲ ሲዘጋጅ መቆየቱ የሚታወቅ ነው፡፡… Read more: ዋና ዋና የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ይዘቶች – ሲጨመቁ
- “የአማራ ክልል ሚሊሻዎች ትጥቅ ይፍቱ በሚል የሚሰራጩ መረጃዎች ‘ባልበላውም ጭሬ ላፍሰው’ ከሚል ቅዠት የተወለደ ቅጥፈት ነው”“የሚሊሻ ኀይሉን በተመለከተ የሚዘዋወረው መረጃ ፍጹም መሠረተ ቢስ ነው” ሲሉ ኮሎኔል ግርማ ገሰሰ አስታወቁ። “ቅጥፈት ነው” ያሉትና በፕሬዚዳንቱ ስምና ፊርማ የተሰራጨው ደብዳቤ የሚሊሻ ሃይሉ ጸጥታ በማስከበሩ ስራ… Read more: “የአማራ ክልል ሚሊሻዎች ትጥቅ ይፍቱ በሚል የሚሰራጩ መረጃዎች ‘ባልበላውም ጭሬ ላፍሰው’ ከሚል ቅዠት የተወለደ ቅጥፈት ነው”
- “የህዝባችንን ድምጽ የሚቀማና የሚያፍን የ’አማራ ስብስብ’ ለአማራ ክልል ተግዳሮት ሆኗል… ትህነግ ዘርፎ እያጋጋዘ ነው” አብን“የትግራይ ተወላጆች ትህነግ ለፈጸመው ወረራ፣ ዘረፋ፣ ማፈናቀልና የግድያ ተግባራት የተቀናጀ የፖለቲካና የሚዲያ ድጋፍ ሰጥተዋል። በተለይም በትግራይ ክልል መቀሌ ከተማ ሮማናት አደባባይ ላይ የተለመደው አይነት የፈንጠዝያ ድጋፍ ሲደረግ… Read more: “የህዝባችንን ድምጽ የሚቀማና የሚያፍን የ’አማራ ስብስብ’ ለአማራ ክልል ተግዳሮት ሆኗል… ትህነግ ዘርፎ እያጋጋዘ ነው” አብን