ግብጽ የህዳሴው ግድብ ከፍተኛ የውሃ እጥረት የሚያስከትል በመሆኑ አለምአቀፍ የሰላምና መረጋጋት ችግር መንስኤ ነው በማለት የጸጥታው ምክር ቤት አጀንዳ እንዲሆን ያቀረበችው ሀሳብ ተቀባይነት እንዳላገኘ ዘናሽናል ኒውስ ዘግቧል።
ግብጽ በተደጋጋሚ የህዳሴው ግድብ በሀገሪቱ ብሔራዊ ጥቅም ላይ አደጋ እንደደቀነባት ስሞታ ስታቀርብ ከመቆየቷም ባሻገር ግድቡን ለማፍረስ ወታደራዊ እርምጃን ጨምሮ ማንኛውንም አማራጭ እንደምትጠቀም መግለጿ የሚታወስ ነው።
በአንፃሩ ኢትዮጵያ ግድቡ በታችኞቹ ተፋሰስ ሀገራት ላይ ጉዳት እንደማያደርስ ብዙ ጊዜ አሳውቃለች። ግብጽ የጸጥታው ምክር ቤት የውሃ ጉዳይ አጀንዳው እንዲያደርግና የህዳሴው ግድብም ዓለም አቀፍ አጀንዳ እንዲሆን ጥያቄ ብታቀርብም ምክር ቤቱ ጉዳዩ የልማት አጀንዳ እንጂ የሰላምና ጸጥታ አለመሆኑን በማስገንዘብ ጥያቄውን ውድቅ አድርጓል።
ሀገሪቱ ባሳለፈነው አንድ ዓመት ብቻ በተደጋጋሚ ጉዳዩን ወደ ጸጥታው ምክር ቤት ለመውሰድ ከፍተኛ ግፊት ማድረጓ የሚታወስ ነው። የጸጥታው ምክር ቤት የግብጽን ጥያቄ ውድቅ በማድረግ ሶስቱ ሃገራት በአፍሪካ ህብረት መሪነት ገንቢና ትብብር በተሞላበት መንገድ በአፋጣኝ ወደ ድርድሩ እንዲመለሱ አሳሰቧል።
በተባበሩት መንግስታት የኢትዮጵያ አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ምክር ቤቱ አለምአቀፍ ሰላምና መረጋጋትን የተመለከቱ ጉዳዮችን ብቻ የማየት ስልጣን እንዳለው በመጥቀስ፤ ጉዳዩ የሚቋጨው በሶስትዮሽ ድርድር ብቻ በመሆኑ ግብጽና ሱዳን ወደ ድርድሩ ፈጥነው እንዲመለሱ መጠየቃቸውንም ናሽናል ኒውስን ጠቅሶ ኢዜአ አመልክቷል።
- Ethiopia Has The Right To Be Included In The Red Sea CouncilByAndrew Korybko – SURVIVE the NEWS State Minister Misganu Arga told the Ethiopian News Agency that “We have the right to be included in the Red Sea Council as most of our trade transactions are made and our ships pass through the Red Sea corridor. Any activities that are underway across this … Read moreContinue Reading
- Frequently Asked Questions About Ethiopia’s Quest For Its Own Red Sea PortByAndrew Korybko – SURVIVE the NEWS Prime Minister (PM) Abiy Ahmed has recently prioritized his country’s long-held quest for reobtaining its own Red Sea port, which has led to lots of fake news about Ethiopia’s intentions. This piece comprises answers to the most frequently asked questions about this policy in … Read moreContinue Reading
- Ongoing negotiations in Dar es salaam showing “positive progress”– Senior gov’t officials join military leaders in Dar es Salaam as ongoing talks with OLA progress positively Addisstandard – Ongoing negotiations between the Ethiopian government and the Oromo Liberation Army (OLA) in Dar es salaam are showing “positive progress” sources close to the mediation team revealed to Addis Standard. The … Read moreContinue Reading