ከ466 ዕርዳታ ጭነው መቀለ ካመሩ ከባድ ተሽከርካሪዎች ትህነግ የለቀቃቸው 38 ብቻ መሆናቸው በተመድ ይፋ ሆነ

የዕርዳታ እህል ለማድረስ ወደ መቀሌ ከተላኩት የጭነት ተሽከርካሪዎች አብዛኞቹ እንዳልተመለሱ የተባበሩት መንግስታት የኢትዮጵያ ቢሮ አስታውቋል። ድርጅቱ ይህን ባስታወቀበት ቅጽበት የነጋገርናቸው እንዳሉት የጭነት ተሽከረካሪዎቹ ወደ ትግራይ ሲጓዙ የደርሶ መልስ ነዳጅ ይዘው እንደሚንቀሳቀሱና የነዳጅ ችግር እንደማይገጥማቸው አመልክተዋል።

ተቀማጭነቱ አዲስ አበባ የሆነው የተባበሩት መንግስታት የኢትዮጵያ ቢሮ በቲውተር ገጹ እንዳመለከተው እስካሁን ወደ ትግራይ ዕርዳታ ቀለብ ጭነው ከተጓዙእት 466 የጭነት መኪኖች ውስጥ ወደ መሃል አገር የተመለሱት38 ብቻ ናቸው።

በዓለም ምግብ ፕሮግራም በኩል የዕርዳታ ዕህል እንዲያደርሱ እስካሁን466 የጭነት ተሽከርካሪዎች መቀሌ ቀለብ አራግፈው የተመለሱት 38 ብቻ መሆናቸው በስራው ላይ እክል እንደሚሆነበት አመልክቷል።

በሳምንቱ መጀመሪያ ወደ ትግራይ ካቀኑት ሳምንት 149 ተሽከርካሪዎችን 428 የጭነት መኪኖች ሳይመለሱ መቅረታቸውን ያመለከተው የተባበሩት መንግስታት የአዲስ አበባ ቢሮ፣ የተሽከርካሪዎቹ አለመመለስ ዕርዳታ ለተጎጂዎች የማድረስ ስራውን አስቸጋሪ እንዳደረገበትም ይፋ ተናግሯል። ይሁን እንጂ አላወገዘም ወይም ድርጊቱን በምን መልኩ እንደሚያየው አላስታወቀም።

ያነጋገርናቸው የእርዳታ ዕህል ስርጭት ዘርፍ ውስጥ በቅርብ የሚሰሩ እንዳሉት የጭነት መኪኖቹ የጫኑትን አራግፈው ላለለመመለስ ምንም ምክንያት ሊቀርብባቸው እንደማይችል ነው።

ነዳጅ የደርሶ መልስ እንደሚሞሉ፣ ይህም የተለመደ ተግባራቸው እንደሆነ፣ ባይሆንም የትግራይን ወቅታዊ ሁኔታ ስለሚረዱ ተዘጋጅተው እንደሚሄዱ አመልክተዋል። ከዚህ ውጭ የቴክኒክ ችግር ቢያጋጥም እንኳን ከ466 ተሽከርካሪ፣ 428 ሊበላሽ እንደማይችል አስረድተዋል።

የተባበሩት መንግስታት እንዳሳሰበው ጠቅሶ ያሰራጨውን መረጃ ተከትሎ አዲስ ዘመን “አሸባሪው ህወሓት ተሽከርካሪዎችን በመውሰድ ለጥፋት ተግባሩ መፈፀሚያ እያዋላቸው እንደሆነ የሚያሳዪ መረጃዎች ከሳምንታት በፊት ሲወጡ ነበር” ብሏል። ካልፈው ሁለት ሳምንት ጀምሮ ትህነግ ለርዳታ የሚሄዱ ከባድ መኪኖችን ለወታደራዊ ተግባር እንደሚጠቀምባቸው ሲገለጽ ነበር።

See also  Survivors of TPLF attack in Amhara describe gang rape, looting and physical assaults

የተባበሩት መንግስታት ይፋ ላደረገው መረጃ ትህነግ በይፋ የሰጠው ምላሽ ይህ እስከታተመ ድረስ አልተሰማም።

Leave a Reply