አዲስ አበባ ከ27 ሺህ በላይ ዘብ አደራጀች

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በወንጀል መከላከል ያሰለጠናቸውን ከ27 ሺህ በላይ በጎ ፈቃደኞችን አስመረቀ።የአካባቢ ሠላምና ፀጥታን ለማስጠበቅ መሰረታዊ የፖሊስ ስልጠና የወሰዱ 27 ሺህ 540 በጎ ፍቃደኛ ወጣቶች ምረቃ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ተከናውኗል።ወጣቶቹ በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንና በሌሎች ተቋማት አስተባባሪነት “እኔ ለከተማዬ ሠላም ዘብ ነኝ” በሚል መሪ ሃሳብ ስልጠናቸውን ተከታትለዋል፡፡
ስልጠናው በወንጀል መከላከል፣ በስነምግባር፣ በጎ ፍቃደኝነት፣ የሠላም እሴት ግንባታ እና ሁለንተናዊ ሠላም፣ በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ነው የተሰጠው።በአበበ ቢቂላ መታሰቢያ ስታዲየም በተካሄደው የምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል ሀላፊ አቶ መለሰ አለሙ፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽነር ጌቱ አርጋውና የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
Related posts:
የፓትሪያርኩ የውጭ ጉዞና - "ተቀነባብሯል" የሚባለው ሴራ እያነጋገረ ነው
በአፍሪካ ቀንድ የአሜሪካ ልዩ መልዕከተኛ ራሳቸውን አሰናበቱ፤ ለአራተኛ ጊዜ የተሰማው ስንብት አነጋግሪ ሆኗል
መከላከያ ምዕራብና ምስራቃ ወለጋን እያጸዳ ነው፤ በቤጊ ወደ ካምፕነት በተቀየረ ት.ቤት የነበረ የሸኔ ድርጅት ተደመሰሰ - ሸኔ አላስተባበለም
"ሚናችንን እንለይ" እንቅስቃሴ በኢትዮጵያ ሊጀመር ነው
በተሻለ ጥቅም ለትህነግ ነዳጅ በበርሜል ይሸጋገራል፤ ወልደያና ቆቦ ችግሩ ተባብሷል
Are There TPLF Ethiopia Insurgency Training & Support Operations In Uganda?
ቻናል 29 ትግራይና የታደሰ ወረዳ "የጦርነት ዝግጅት ጨርሰናል" ዜና
አሸባሪው - ህፃናቶችንና አዛውንቶችን በማስገደድ እንደሚማግድ እጃቸውን ለምዕ.ዕዝ የሰጡ ወዶ ገቦች ተናገሩ