የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትርአቶ ቀጀላ መርዳሳ የሥራ ርክክብ አደረጉ

የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሆነው የተሾሙት አቶ ቀጀላ መርዳሳ ከቀድሞው የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ጋር የሥራ ርክክብ አድርገዋል፡፡
ለአዲሱ ሚኒስትርም የቀድሞዋ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር የነበሩት ዶ.ር ኂሩት ካሳው እና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡
በርክክቡ ወቅትም ለሚኒስትሩ ስለ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር አደረጃጀትና እየተሠሩ ስላሉ ሥራዎች እንዲሁም ለወደፊት የታቀዱ እቅዶች በዶ.ር ኂሩት ካሳው ማብራሪያ ተደርጎላቸዋል፡፡
አቶ ቀጀላ መርዳሳ ፥ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሆነው በመመደባቸው የተሰማቸውን ደስታ የገለፁ ሲሆን የኢትዮጵያን ገፅታ ሊቀይር የሚችል ሥራን ለመሥራት የተጣለባቸውን ሀገራዊ ኃላፊነት ካለው አመራርና ሠራተኛ ጋር በመወያየት እንደሚወጡ ተናግረዋል።
ሚኒስትሩ ፥ የሚኒስቴሩ አመራሮች ላደረጉላቸው አቀባበል አመስግነዋል፡፡
ምንጭ፦ ባህል እና ቱሪዝም ሚኒስቴር
Related posts:
«ድርድር አያዋጣንም ሀገሪቷን ማተራመስ አለብን» ታዋቂው ግብጻዊ ፓለቲከኛ
ስምንት የነዳጅ ቦቴዎች ተወረሱ
ሱዳን ትሪቡን ያሰራጨው አሳሳች ምስል!
ከትግራይ የመጡ የሽብር ቡድኑ አባላት በቁጥጥር ሥር ዋሉ
የጌታቸው አሰፋ ፍርድ
“ጠላት አርፎ እንደማይተኛ ታውቆ ለየትኛውም ተጋድሎ ራስን ማዘጋጀት” አማራ ክልል
የፓትሪያርኩ የውጭ ጉዞና - "ተቀነባብሯል" የሚባለው ሴራ እያነጋገረ ነው
በአፍሪካ ቀንድ የአሜሪካ ልዩ መልዕከተኛ ራሳቸውን አሰናበቱ፤ ለአራተኛ ጊዜ የተሰማው ስንብት አነጋግሪ ሆኗል