አስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ ዕዝ «ነጻ በወጡ አካባቢዎች የጸጥታ ችግር በሚፈጥሩ አካላት ላይ፣ ሕጋዊ ርምጃ እንዲወስድ ታዝዟል»

ከአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ ዕዝ የተሰጠ መግለጫ ቁ.6
ታኅሣሥ 14 ቀን 2014 ዓም
የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ ዕዝ ማምሻውን ባደረገው ስብሰባ የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ አፈጻጸሙን ገምግሟል፡፡ በግምገማውም በግንባር ለተገኘው ድል የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ጉልበታቸውን፣ ዕውቀታቸውን፣ ሞያቸውንና ገንዘባቸውን ለሀገራቸው ሳይሰስቱ በመስጠት የፈጸሙት የደጀንነት ገድል አኩሪ መሆኑን ተመልክቷል፡፡ ለዚህ የሕዝባችን ከፍተኛ አስተዋጽዖ የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ ዕዙ ምስጋና ያቀርባል፡፡
የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ ዕዙ የተገኙ ድሎቻችንን ዘላቂና አስተማማኝ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ሲሆን፣ ለዚህም በማኅበረሰቡ፣በአስተዳደር አካላትና በጸጥታ አካላት መወሰድ የሚገባቸውን ተግባራት በመለየት የሚከተሉትን ትእዛዛት ሰጥቷል፡፡
- ከሕዝብ ችግር ለመጠቀም የሚፈልጉ አንዳንድ አካላት፣ ወደ ሀገር ቤት የሚመጣውን የዳያስፖራ ማኅበረሰብ ምክንያት አድርገው ምክንያታዊ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ ለማድረግ መነሣሣታቸው ተደርሶበታል፡፡ ይህ ደግሞ ድኻውን የኀብረተሰብ ክፍል ስለሚጎዳ በእነዚህ ሕገ ወጥ አካላት ላይ መንግሥት አስፈላጊውን ቁጥጥርና ሕግ የማስከበር ተግባር እያከናወነ ነው፡፡ በመሆኑም በየአካባቢው በመሠረታዊ ፍጆታዎችና አገልግሎቶች ላይ ኢኮኖሚያዊ ምክንያት የሌለው የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉና ያለ አግባብ በሚያከማቹ አካላት ላይ፣ የንግድ ቢሮዎችና የጸጥታ አካላት አስፈላጊውን ርምጃ እንዲወስዱ ታዝዘዋል፡፡
- ከአሸባሪው ሕወሐት ነጻ በወጡት አካባቢዎች አስተዳደርን መልሶ የማቋቋምና መሠረታዊ የኅብረተሰብ ችግሮችን በመፍታት ረገድ ያለው እንቅስቃሴ ወጥ በሆነ ሁኔታ እየተተገበረ አለመሆኑን ገምግሟል፡፡ በዚህም ምክንያት የጸጥታ ችግሮችና የወንጀል ተግባራት ነጻ የወጣውን ማኅበረሰብ እያማረሩት ነው፡፡ በመሆኑም የአማራ ክልል መንግሥት የየአካባቢውን አስተዳደር በአስቸኳይ በብቁ አመራሮች እንዲያደራጅ፤ መደበኛ የፖሊስ ኃይሎችም የተጠናከረ ሥራ እንዲጀምሩ እንዲያደርግ፣ እነዚህን ለማድረግ ባልተቻለባቸው ቦታዎች የሚንቀሳቀስ የመከላከያ ኃይል፣ ነጻ በወጡ አካባቢዎች የጸጥታ ችግር በሚፈጥሩ አካላት ላይ፣ ሕጋዊ ርምጃ እንዲወስድ ታዝዟል፡፡
- አሸባሪው ኃይል ተቆጣጥሯቸው በነበሩ አካባቢዎች፣ ባደራጃቸው ሕገ ወጥ መዋቅሮች አማካኝነት፤ የቀደመው አስተዳደር ይጠቀምባቸው የነበሩትን ማኅተሞች በመጠቀምና አዳዲስ ሕገ ወጥ ማኅተሞችን በመቅረጽ ሕገ ወጥ መታወቂያዎችን መስጠቱ፤ የተለያዩ ሕገ ወጥ ሰነዶችን ማዘጋጀቱ ተደርሶበታል፡፡ በመሆኑም በየአካባቢው የተቋቋሙ የመስተዳድር አካላትና የጸጥታ ኃይሎች አሸባሪው ሕወሐት ያስቀረጻቸውን ማኅተሞች፣ መታወቂያዎችና ሌሎች ሰነዶች እንዲያመክኑ ታዝዘዋል፡፡
- ነጻ በወጡ አካባቢዎች ሕገ ወጥ የጦር መሣሪያ ዝውውሮችና ጠላት አንጠባጥቧቸው የሄዱ የጦር መሣሪያዎች በመኖራቸው ለሕዝብ ሰላምና ደኅንነት ሥጋት ሊሆኑ የሚችሉ አዝማሚያዎች መኖራቸው ተደርሶበታል፡፡ በመሆኑም የየአካባቢው ልዩ ኃይልና ፖሊስ በአስቸኳይ እነዚህ ጉዳዮች ሥርዓት እንዲያሲዙ ታዝዘዋል፡፡ እነዚህ ኃይሎች ባልተጠናከሩባቸው አካባቢዎችም የመከላከያ ኃይል አስፈላጊውን ርምጃ እንዲወስድ ትእዛዝ ተሰጥቷል፡፡
የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ ዕዝ
- «ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የኢዜማ መሪ ሆነው ስለተመረጡ እንኳን ደስ ያለዎት» አንዱዓለም አራጌከተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች አያሌ ኪሎ ሜትሮች አቆራርጣችሁ ለሁለት ቀናት በዚህ ታላቅ ጉባዔ ላይ የታደማችሁ የተከበራችሁና…
- «ድርድር አያዋጣንም ሀገሪቷን ማተራመስ አለብን» ታዋቂው ግብጻዊ ፓለቲከኛታዋቂው ግብጻዊ ፓለቲከኛ ኢትዮጵያን ስለማተራመስ – ኢትዮጵያ ውስጥ ኤምባሲ አያስፈልገንም – ፍትሃዊ የውሃ ድርድር የሚለው…
- ስምንት የነዳጅ ቦቴዎች ተወረሱየአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ ሆን ብለው የነዳጅ እጥረት እንዲከሰትና ከመንግስት የተሰጠውን መመሪያና ደንብ ችላ…
- ሱዳን ትሪቡን ያሰራጨው አሳሳች ምስል!EthiopiaCheck Fact Check ሱዳን ትሪቡን የተባለ ድረ-ገጽ በትናንትናው ዕለት ‘Sudanese forces attack Ethiopian troops in…
- ከትግራይ የመጡ የሽብር ቡድኑ አባላት በቁጥጥር ሥር ዋሉከትግራይ ክልል የመጡ የሽብር ቡድኑ አባል የሆኑ ሁለት የልዩ ኃይል አባላት በቁጥጥር ስር ዋሉ። እነዚህ…
- ታዳጊ ሀገራት ከሩሲያ ማዳበሪያ እንዳይሸምቱ የአውሮፓ ህብረት ፕሮፖዛልአውሮፓ ህብረት ታዳጊ ሀገራት ከሩሲያ የሚያደርጉትን ግዢ በማገድ ግንኙነታቸውን ወደ ሌሎች ሀገራት ያደርጉ ዘንድ በህብረቱ…
- የጌታቸው አሰፋ ፍርድየቀድሞ የብሔራዊ መረጃ ደህንነት አገልግሎትዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው አሰፋ በ18 አመት ጽኑ እስራት በ20 ሺህ…
- “ጠላት አርፎ እንደማይተኛ ታውቆ ለየትኛውም ተጋድሎ ራስን ማዘጋጀት” አማራ ክልልጠላት አርፎ እንደማይተኛ ታውቆ ለየትኛውም ተጋድሎ ራስን ማዘጋጀት እንደሚገባ የአማራ ክልል መንግሥት አስታወቀ። የአማራ ክልል…
- የአማራ ክልል ሚሊሻ ጽሕፈት ቤት “ሚሊሻው ዝግጁ ነው”አሸባሪው ትህነግ ሕዝብ እየሰበሰበ ለዳግም ጦርነት እየተዘጋጀ በመሆኑ ቡድኑን ለማሳፈርና ለማንበርከክ በተጠንቀቅ መጠበቅ እንደሚገባ የአማራ…
- ህይወት በማጥፋት ወደ ኬኒያ ሸሽተው የነበሩ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉየአንድ ቻይናዊ ዜጋን ህይወት በማጥፋት ወደ ኬኒያ ሸሽተው የነበሩ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ በአዲስ አበባ…
- የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጭፍጨፋ በጽኑ አውግዟል- ሕግ የማስከበር እርምጃ አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስቧልየኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት :-– በንጹሐን ዜጐች ላይ የደረሰውን ጭፍጨፋ በጽኑ አውግዟል– ሕግ የማስከበሩ…
- የፓትሪያርኩ የውጭ ጉዞና – “ተቀነባብሯል” የሚባለው ሴራ እያነጋገረ ነውየኢትዮጵያ ፓትሪያርክ ብፁዕ አቡነ ማትያስ እግራቸውን ላይ “ገጠመኝ” ባሉት ችግር የሚፈልጓቸውን መርጠው ወደ አሜሪካ ለመጓዝ…
Related posts:
«ድርድር አያዋጣንም ሀገሪቷን ማተራመስ አለብን» ታዋቂው ግብጻዊ ፓለቲከኛ
ስምንት የነዳጅ ቦቴዎች ተወረሱ
ሱዳን ትሪቡን ያሰራጨው አሳሳች ምስል!
ከትግራይ የመጡ የሽብር ቡድኑ አባላት በቁጥጥር ሥር ዋሉ
የጌታቸው አሰፋ ፍርድ
“ጠላት አርፎ እንደማይተኛ ታውቆ ለየትኛውም ተጋድሎ ራስን ማዘጋጀት” አማራ ክልል
የፓትሪያርኩ የውጭ ጉዞና - "ተቀነባብሯል" የሚባለው ሴራ እያነጋገረ ነው
በአፍሪካ ቀንድ የአሜሪካ ልዩ መልዕከተኛ ራሳቸውን አሰናበቱ፤ ለአራተኛ ጊዜ የተሰማው ስንብት አነጋግሪ ሆኗል