” ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን መገንባት የምንችለዉ በትጥቅ ትግል ሳይሆን በበሰለና በሰለጠነ ዉይይት ብቻ ነዉ። “- አቶ ሌንጮ ለታ
በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት የሚዘጋጀዉ 18ኛዉ ዙር የጉሚ በለል የዉይይት መድረክ ” የብሔራዊ ዉይይቱ አንኳር ጉዳዮችና ሃገራዊ ፋይዳዉ” በሚል ርዕስ ተካሄዷል።
ለዉይይት መድረኩ የተዘጋጀዉን የመወያያ ጽሁፍ ያቀረቡት በኦሮሞ ፖለቲካ ዉስጥ ትልቅ ከበሬታ የሚሰጣቸዉ አንጋፋዉ ፖለቲከኛ አቶ ሌንጮ ለታ ሲሆኑ በሃገራዊ ወይይቱ አስፈላጊነትና በዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ዙሪያ አንኳር ነጥቦችን አንስተዋል።
ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን መገንባት የሚቻለዉ በትጥቅ ትግል ሳይሆን በበሰለና በሰለጠነ ወይይት ብቻ ነዉ ያሉት አወያዩ ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን ለመገንባት ከጦርነት ይልቅ ሰላማዊ ወይይት ተመራጭ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ሃገራዊ ዉይይቱ ለኦሮሞ ህዝብ በጣም አስፈላጊ መሆኑን የገለጹት አወያዩ ሃገራዊ ዉይይቱ በርካታ ድምጾችና ፍላጎቶች የሚንጸባረቁበትና የሚሰሙበት ሊሆን ይገባል ብለዋል።
እኩልነት በሌለበት አንድነትን መፍጠር አይችልም ያሉት አወያዩ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን ለመፍጠር ሁሉም ብሔር ብሔረሰቦች ራሳቸዉን የሚመለከቱባትን ኢትዮጵያን መገንባት ይገባል ብለዋል።
ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን በሂደት እንጂ በአንድ ጊዜ መገንባት አይቻልም ያሉት አቶ ሌንጮ ለታ እንከን የሌለበት ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን መፈለግ የተሳሳተ አስተሳሰብ ነዉ ብለዋል።
አንዳንድ የዉይይቱ ተሳታፊዎችም ያለፉት ስርዓቶች ሲከተሉት የነበረዉ ፖለቲካዊ አስተሳሰብና ትርክት በሕዝቦች መካከል ልዩነት እንዲሰፋና አለመግባባት እንዲፈጠር ምክንያት ሆኗል ብለዋል።
ያለፉት ስርዓቶች በህዝቡ መካከል ጥለዉ ያለፉትን የተዛቡና ተቀባይነት የሌላቸዉ ትርክቶችንና አስተሳሰቦችን በማረም ህብረ ብሄራዊ አንድነትን ለመገንባት ሃገራዊ ዉይይቱ ትልቅ ድርሻ አለዉ ብለዋል።
ፖለቲከኞች: ጋዜጠኞች: አርቲስቶችና ምሁራን ለሃገራዊ ዉይይቱ ስኬት የድርሻቸዉን ሊወጡ እንደሚገባም ገልጸዋል።
ተሳታፊዎቹን ያወያዩት የኦሮሚያ ዳያስፖራ ዳይሬክተር አቶ አሚን ጁንዲ ሲሆኑ በዉይይት መድረኩ ላይ ታዋቂ የኦሮሞ ፖለቲከኞች: የሚዲያ አመራሮችና ጋዜጠኞች: አትሌቶች: አርቲስቶችና ሌሎች ተሳታፊዎች ተገኝተዋል። via OBN
ወንድማገኝ አሰፋ
- “የአማራ ክልል ሚሊሻዎች ትጥቅ ይፍቱ በሚል የሚሰራጩ መረጃዎች ‘ባልበላውም ጭሬ ላፍሰው’ ከሚል ቅዠት የተወለደ ቅጥፈት ነው”“የሚሊሻ ኀይሉን በተመለከተ የሚዘዋወረው መረጃ ፍጹም መሠረተ ቢስ ነው” ሲሉ ኮሎኔል ግርማ ገሰሰ አስታወቁ።… Read more: “የአማራ ክልል ሚሊሻዎች ትጥቅ ይፍቱ በሚል የሚሰራጩ መረጃዎች ‘ባልበላውም ጭሬ ላፍሰው’ ከሚል ቅዠት የተወለደ ቅጥፈት ነው”
- “የህዝባችንን ድምጽ የሚቀማና የሚያፍን የ’አማራ ስብስብ’ ለአማራ ክልል ተግዳሮት ሆኗል… ትህነግ ዘርፎ እያጋጋዘ ነው” አብን“የትግራይ ተወላጆች ትህነግ ለፈጸመው ወረራ፣ ዘረፋ፣ ማፈናቀልና የግድያ ተግባራት የተቀናጀ የፖለቲካና የሚዲያ ድጋፍ ሰጥተዋል።… Read more: “የህዝባችንን ድምጽ የሚቀማና የሚያፍን የ’አማራ ስብስብ’ ለአማራ ክልል ተግዳሮት ሆኗል… ትህነግ ዘርፎ እያጋጋዘ ነው” አብን
- “ትህነግ ብልፅግናን ለመቀላቀል በድርድር ላይ ነው ” የዜናው ሰም፣ ወርቅና የትህነግ ‘ ሃሰት ነው’ ማስተባበያለአንድ ቀን ከጮኸና አየሩን ሁሉ ከተቆጣጠረ በሁዋላ ውሃ የተቸለሰበት “ሕወሓት ብልፅግናን ለመቀላቀል በድርድር ላይ… Read more: “ትህነግ ብልፅግናን ለመቀላቀል በድርድር ላይ ነው ” የዜናው ሰም፣ ወርቅና የትህነግ ‘ ሃሰት ነው’ ማስተባበያ
- National Dialogue, Transitional Justice And Rehabilitation Process Pillars of Lasting Peace, Prosperity: CouncilThe Ethiopian National Security Council has issued a statement on latest developments in the… Read more: National Dialogue, Transitional Justice And Rehabilitation Process Pillars of Lasting Peace, Prosperity: Council
- ቀሲስ በላይ በተጠረጠሩበት ወንጀል ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀረቡ ዋስትና ተከለከሉየፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት አራዳ ምድብ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት የቀሲስ በላይ መኮንንን ጨምሮ የ3… Read more: ቀሲስ በላይ በተጠረጠሩበት ወንጀል ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀረቡ ዋስትና ተከለከሉ
- መንግስት ክትግስት በኋላ የሚከሰት ሕግ ማስከበር ውጤቱ አስከፊ እንደሚሆን አስታውሶ ጦርነት ናፋቂዎች አደብ እንዲገዙ አሳሰበ“ካለፈው ስሕተታቸው ሳይማሩ ዛሬም ተመሳሳይ ችግር ለመፍጠር የሚከጅሉትን ሁላችንም ተባብረን አደብ ማስገዛት ይኖርብናል። ከትዕግሥት… Read more: መንግስት ክትግስት በኋላ የሚከሰት ሕግ ማስከበር ውጤቱ አስከፊ እንደሚሆን አስታውሶ ጦርነት ናፋቂዎች አደብ እንዲገዙ አሳሰበ
- Somaliland offended by G7 referring the Republic of Somaliland as “Somaliland Region of Somalia” The Republic of Somaliland, is a sovereign state with its own laws and constitution,… Read more: Somaliland offended by G7 referring the Republic of Somaliland as “Somaliland Region of Somalia”