የተመድ ሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት በ08/04/2014 ዓ/ም በአብላጫ ድምፅ ያሳለፈውን ውሳኔ (ዓለም አቀፍ የመርማሪ ቡድን በኢትዮጵያ እንዲሰማራ) ኢትዮጵያ እንደማትቀበለው ፤ እንደማታስፈፅም፤ የትኛውም አይነት ትብብር እንደማታደርግ ማሳወቋ ይታወሳል።
የተመርማሪ ሀገር ፍቃድ በሌለበት የመርማሪ ቡድኑ ዕጣ ምን ሊሆን ይችላል ? ኢትዮጵያ ተገዳ መርማሪዎችን የምታስገናግድበት አሰራር ወይም ዓለም አቀፍ ህግ አለ ?
በዚህ ጉዳይ ለቪኦኤ አስተያየታቸውን የሰጡት ዶክተር አደም ካሴ (በተለይ በአፍሪካ የህግ እና ፖለቲካ ጉዳዮች ተንታኝ) ተከታዩን ብለዋል ፦
” በዓለም አቀፍ ህግ ይሄን ኮሚሽን በሚመለከት አንድ ሀገር ውስጥ ሊገባ የሚችለው / በሀገሪቱ ገብቶ ሊመረምር የሚችለው በሀገሪቱ ፍቃድ ከተሰጠው ብቻ ነው።
ኢትዮጵያን ሊያስገድዳት የሚችል ስርዓት የለም። ምንም እንኳን የህግ ስርዓት ባይኖርም በፖለቲካ ደረጃ ጫና ሊያመጣ የሚችል ፤ ምን የምትደብቁት ነገር አለ ? እየተባለ ፖለቲካዊ ጫናዎችን ሊያመጣብን ይችላል።
በህግ በኩል የኢትዮጵያ መንግስት እስካልተስማማ ድረስ ወደ ሀገር የመግባት መብት የላቸውም።
ሌላው ጉዳይ በአጠቃላይ በዓለም ደረጃ ከውሳኔ ሰጪ አካላት በተጨማሪ እነዙህ ውሳኔ አካላትን እየተጠቀሙ አንዳንድ ሀገራት እነሱ የሚደግፉትን አቋም ለማራመድ ይጠቀሙበታል።
በተለይ አሜሪካ እና ምዕራባውያን ኢትዮጵያ ይሄን ቡድን የማታስገባ ከሆነ አንዳንድ ጫናዎች ለማስረግ ለምሳሌ ማዕቀቦችን ለመጫን እና ግፉቶችን ለማድረግ ሊጠቀሙበት ይችላሉ።
ኢትዮጵያ በህግ ደረጃ ወደ ኢትዮጵያ ውስጥ የማስገባት ግዴታ ባይኖርባትም በተመድም ከዛም አልፎ ውሳኔውን የሚደግፉ ሀገራት ምዕራባውያን ሀገራትም ያንን ተጠቅመው ጫና ሊያደርጉ ይችላሉ።
ነገር ግን ወደ ኢትዮጵያ አይገቡም ማለት ምርመራውን ማድረግ አይችሉም ማለት አይደለም። ምርመራውን ማካሄድ ይችላሉ፤ ይቀጥላሉ በስልክም በሌላም መንገድ አካሂደው አለ የሚሉትን መረጃ ለምክር ቤቱ ያቀርባሉ። “
- “የአማራ ክልል ሚሊሻዎች ትጥቅ ይፍቱ በሚል የሚሰራጩ መረጃዎች ‘ባልበላውም ጭሬ ላፍሰው’ ከሚል ቅዠት የተወለደ ቅጥፈት ነው”“የሚሊሻ ኀይሉን በተመለከተ የሚዘዋወረው መረጃ ፍጹም መሠረተ ቢስ ነው” ሲሉ ኮሎኔል ግርማ ገሰሰ አስታወቁ። “ቅጥፈት ነው” ያሉትና… Read more: “የአማራ ክልል ሚሊሻዎች ትጥቅ ይፍቱ በሚል የሚሰራጩ መረጃዎች ‘ባልበላውም ጭሬ ላፍሰው’ ከሚል ቅዠት የተወለደ ቅጥፈት ነው”
- “የህዝባችንን ድምጽ የሚቀማና የሚያፍን የ’አማራ ስብስብ’ ለአማራ ክልል ተግዳሮት ሆኗል… ትህነግ ዘርፎ እያጋጋዘ ነው” አብን“የትግራይ ተወላጆች ትህነግ ለፈጸመው ወረራ፣ ዘረፋ፣ ማፈናቀልና የግድያ ተግባራት የተቀናጀ የፖለቲካና የሚዲያ ድጋፍ ሰጥተዋል። በተለይም በትግራይ ክልል… Read more: “የህዝባችንን ድምጽ የሚቀማና የሚያፍን የ’አማራ ስብስብ’ ለአማራ ክልል ተግዳሮት ሆኗል… ትህነግ ዘርፎ እያጋጋዘ ነው” አብን
- “ትህነግ ብልፅግናን ለመቀላቀል በድርድር ላይ ነው ” የዜናው ሰም፣ ወርቅና የትህነግ ‘ ሃሰት ነው’ ማስተባበያለአንድ ቀን ከጮኸና አየሩን ሁሉ ከተቆጣጠረ በሁዋላ ውሃ የተቸለሰበት “ሕወሓት ብልፅግናን ለመቀላቀል በድርድር ላይ ነው” የሚለው የዋዜማ… Read more: “ትህነግ ብልፅግናን ለመቀላቀል በድርድር ላይ ነው ” የዜናው ሰም፣ ወርቅና የትህነግ ‘ ሃሰት ነው’ ማስተባበያ
- National Dialogue, Transitional Justice And Rehabilitation Process Pillars of Lasting Peace, Prosperity: CouncilThe Ethiopian National Security Council has issued a statement on latest developments in the country. In its… Read more: National Dialogue, Transitional Justice And Rehabilitation Process Pillars of Lasting Peace, Prosperity: Council
- ቀሲስ በላይ በተጠረጠሩበት ወንጀል ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀረቡ ዋስትና ተከለከሉየፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት አራዳ ምድብ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት የቀሲስ በላይ መኮንንን ጨምሮ የ3 ግለሰቦችን ጊዜ ቀጠሮ… Read more: ቀሲስ በላይ በተጠረጠሩበት ወንጀል ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀረቡ ዋስትና ተከለከሉ
- መንግስት ክትግስት በኋላ የሚከሰት ሕግ ማስከበር ውጤቱ አስከፊ እንደሚሆን አስታውሶ ጦርነት ናፋቂዎች አደብ እንዲገዙ አሳሰበ“ካለፈው ስሕተታቸው ሳይማሩ ዛሬም ተመሳሳይ ችግር ለመፍጠር የሚከጅሉትን ሁላችንም ተባብረን አደብ ማስገዛት ይኖርብናል። ከትዕግሥት በኋላ የሚከሠት ሕግ… Read more: መንግስት ክትግስት በኋላ የሚከሰት ሕግ ማስከበር ውጤቱ አስከፊ እንደሚሆን አስታውሶ ጦርነት ናፋቂዎች አደብ እንዲገዙ አሳሰበ
- Somaliland offended by G7 referring the Republic of Somaliland as “Somaliland Region of Somalia” The Republic of Somaliland, is a sovereign state with its own laws and constitution, reaffirmed by the… Read more: Somaliland offended by G7 referring the Republic of Somaliland as “Somaliland Region of Somalia”
- ” በትጥቅ ትግል ውስጥ ያሉ ወገኖቻችን አሁንም ሳይመሽ ቶሎ ወደ ድርድሩ እንዲገቡ በትህትና እንጠይቃለን ” ፕ/ር መስፍን አርአያየኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በሌላ መንገድ እየታገሉ ይገኛሉ ያላቸው አካላት ወደ ምክክር መድረኩ እንዲገቡ ጥሪ አቀረበ። ኮሚሽኑ… Read more: ” በትጥቅ ትግል ውስጥ ያሉ ወገኖቻችን አሁንም ሳይመሽ ቶሎ ወደ ድርድሩ እንዲገቡ በትህትና እንጠይቃለን ” ፕ/ር መስፍን አርአያ
- የቡድን ሰባት አገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በኢትዮጵያ ጉዳይ የይሁንታና የስጋት ቅልቅል መግለጫ ሰጡየቡድን ሰባት ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በተለያዩ ጉዳዮች ላይ መግለጫ ሲሰጡ እግረመንገዳቸውን ኢትዮጵያን አስመልክቶ በበጎ ጎኑንና በስጋት… Read more: የቡድን ሰባት አገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በኢትዮጵያ ጉዳይ የይሁንታና የስጋት ቅልቅል መግለጫ ሰጡ