"Helen Clark" የቀድሞው ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊና በ"WHO" የአሸባሪው ትህነግ ቃል አቀባይ የሆነው የዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም የቅርብ ወዳጅ ነች። እ ኤ አ ከ1999-2008 የኒውዝላንድ 37ኛ ጠ/ሚኒስትር፣ ከ2009-2017 ደግሞ የተባበሩት መንግስታት አድሚኒስትሬተር ነበረች።
ታዲያ የአሸባሪው የትህነግ ሰዎች የቀኝ እጅ የሆነችው “Helen Clark” ዘ ጋርዲያን ላይ ከሌሎች አጋሮቿ ጋር በመሆን…አዲስ አበባን ጨምሮ በሌሎቹም የኢትዮጵያ አካባቢዎች በትግራይ ብሔር ላይ ጄኖሳይድ ሊፈፀም ምልክቶች እየታዩ ነው… በማለት ዘ ጋርዲያንን በውሸት ቅርሻቷ ለቅልቀዋለች(ሊንኩ በኮመንት ሳጥን ውስጥ ይገኛል)። ይህ በነዚህ በአፍቃሪ ትህነግ አንጃዎች የተለቀቀው መጣጥፍ ሙሉ በሙሉ የተዘጋጀው በቴዎድሮስ አድሃኖም መሆኑ ግልፅ ነው። ዘለግ ባለ ዐ/ገር ለዓለም አቀፉ ሕብረተሰብ ቀጭን ትዕዛዝ የሚያስተላልፍ የሚመስለው የመጣጥፉ ርዕስ “The Warning Signs are there for genocide in Ethiopia–the World must act to.prevent it.” የሚል ነው። በእኔ በኩል ለ”ዘ-ጋርዲያን” ይህን ሽፍጥ በተመለከተ ምላሽ ተልኮላቸዋል። የምትችሉ እውነታውን በተመለከተ በ opinion@theguardian.com ኢ-ሜይል አድርጉላቸው። በ”WHO” የአሸባሪው ትህነግ ቃል አቀባይ የሆነው ቴዎድሮስም በእነ “Helen Clark” ስም የቀረበውን የራሱን ፅሁፍ ስላጋራ ገብታችሁ በ twitter@Dr Tedros የበኩላችሁን ምላሽ ስጡ።
ይህን የምናደርገው ያለ ምክንያት አይደለም። በአሁኑ ወቅት አሸባሪው ትህነግ በጦር ሜዳ ያጣውን ድል በዓለም አቀፍ መድረኮች ለማግኘት ተፍ ተፍ እያለ ይገኛል። በጄኖሳይድ ስም የኢትዮጵያን መንግስት በዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት (ICJ) ለማቆምና ከተሳከለትም “Humanitarian Referendum” አከናውኖ ትግራይን በእነ አሜሪካ፣ እንግሊዝና ግብፅ አለን ባይነት ለመገንጠል የሞት ሽረት ጥረት እያደረገ ይገኛል። “Humanitarian Referendum” ቀጥሎም “Humanitarian Secession” በስመ ጭቆናና ጂኖሳይድ በተባበሩት መንግስታት ጣልቃ ገብነት ያለ ኢትዮጵያ ፈቃድ በተናጠል ሊወሰን የሚችል የመገንጠል አካሄድ ነው። በእርግጥ ይህን ስልት ተጠቅመው በዓለም አቀፍ ደረጃ የሀገርነት ዕውቅና ያገኙ ሀገራት የሉም…ከባንግላዴሽ በስተቀር። ኮሶቮም ብትሆን እስከአሁን ከፊል የሀገርነት ዕውቅናን ነው ያገኘችው። ለዚህም በዓለም አቀፉ ፍርድ ቤት (ICJ) በኮሶቮ ጉዳይ ዳኞቹ ለሁለት መከፈላቸው በምክንያትነት ይጠቀሳል።
ባለፈው የተባበሩት መንግስታት ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ጋር በጣምራ ባደረጉት ጥናት ትህነግ ቀን ከሌት የሚለፍፈውን ጄኖሳይድ በተመለከተ ትግራይ ውስጥ ምንም ማስረጃ እንዳልተገኘ ሪፖርት ማድረጋቸው ይታወሳል። ሪፖርቱ በተለቀቀበት ወቅት የትህነግ ሠራዊት ወደ አዲስ አበባ እየተቃረበ ስለነበር ለይዘቱ ምዕራባውያን ትኩረት አልሰጡም ነበር። ሆኖም ትህነግ አከርካሪው ተመትቶ ወደ ትግራይ መሸምጠጥ ሲጀምር ምዕራባውያን በአውሮፓ ሕብረት አጋፋሪነት የጄኖሳይድ ትሪክቱን እንደ አዲስ ቀስቅሰውታል…ይህ እንቅስቃሴ ትህነግ የራሱን የሽግግር መንግስት አቋቁሞ ለማካሄድ ያሰበው ሕገመንግስታዊ ሪፍረንደም ሲከሽፍበት በሰብዓዊ ሪፍረንደም (Humanitarian Referendum) ለመተካት የሚደረግ መፍጨርጨር ነው። በወታደራዊ ሜዳ ያጡትን በዲፕሎማሲያዊው ለመቀልበስ የሚደረግ ሩጫ ነው። ከትናንት ወዲያ ቢቢሲ ላይ የቀረበው የትህነግ ጄኔራል ፃዲቃን ገ/ትንሳኤ “የፖለቲካና የዲፕሎማሲ ሂደቶች ከወታደራዊ አካሄዳችን ጋር ሊጣጣሙ አልቻሉም” ያለውን የቤት ሥራ አሁን አሜሪካ፣ እንግሊዝ፣ የአውሮፓ ሕብረትና የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ተረበርበው ሊሰሩለት ደፋ ቀና እያሉለት ነው።
አንድ እውነት ላስቀምጥ፤ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን በጦር ሜዳ የኢትዮጵያን ሕልውና ለማስቀጠል የሕይወት መስዋዕትነት ሁሉ ሳይቀር ከፍሏል። አሁን ተረው የኛ ነው፤ መላ ኢትዮጵያዊያን በሀገር ውስጥም ከሀገር ውጪም ያለን ፤ ትህነግ በጦር ሜዳ ያቃተውን በዲፕሎማሲያዊ መድረክ ለማንበርከክ ከተሳካለትም በስመ ጄኖሳይድ ሪፍረንደም ለማከናወን የሚያደርገውን መፍጨርጨር የምናመክንበት ወቅቱ አሁን ነው። ወንድሞቻችንና እህቶቻችን በሐሩር፣ በውርጭ፣ በደጋት ቁልቁለት ፣ ተራራ በመውጣት በመውረድ የከፈሉትን መስዋዕትነትና ድል እኛ በሶሻል ሚዲያና በ”No.More” እንቅስቃሴ ለመድገም እንደምን ያቅተናል?
Via Getahun Heramo (Nita Color) Fb
- Kenya’s military chief dies in a helicopter crash, Nairobi declares three days of national mourningKenya’s military chief Gen. Francis Ogolla died in a helicopter crash west of the… Read more: Kenya’s military chief dies in a helicopter crash, Nairobi declares three days of national mourning
- U.S. stops UN from recognizing a Palestinian state through membershipCGTN – The United States on Thursday stopped the UN from recognizing a Palestinian… Read more: U.S. stops UN from recognizing a Palestinian state through membership
- Israel launches missile attacks on Iran: reportCGTN – Israeli missiles have hit a site in Iran, ABC News reported late… Read more: Israel launches missile attacks on Iran: report
- ዓለም ባንክና መንግስት በአሜሪካ እየመከሩ ነው፤ ኢትዮጵያ ” የብርን የምንዛሬ አቅም ቀንሱ” ጥያቄ አልተቀበለችምዓለም ባንክና የዓለም ዓቀፉ የገንዘብ ተቋም ኢትዮጵያ የጠቀችውን ብድር ለመፍቀድ ያቀረቡት ዋና ቅድመ ሁኔታ… Read more: ዓለም ባንክና መንግስት በአሜሪካ እየመከሩ ነው፤ ኢትዮጵያ ” የብርን የምንዛሬ አቅም ቀንሱ” ጥያቄ አልተቀበለችም
- ቀሲስ በላይ ከ 6.5 ሚሊዮን ዶላር በላይ ህገወጥ የገንዘብ ዝውውር ወንጀል ታስረው ፍርድ ቤት ቀረቡMore stories እነ ስብሃት ነጋ በትግራይ ክልል ለመዳኘት ያቀረቡት ጥያቄ ውድቅ ሆነ – ቅድመ… Read more: ቀሲስ በላይ ከ 6.5 ሚሊዮን ዶላር በላይ ህገወጥ የገንዘብ ዝውውር ወንጀል ታስረው ፍርድ ቤት ቀረቡ
- “ንገሩዋቸው፣ ምከሩዋቸው” ሌላ ጦርነት እብደትሰሞኑንን ለይቶለት ይፋ ሆነ እንጂ ውስጥ ውስጡን የጦርነት እንቅስቃሴ ሲደረግ እንደነበር መረጃዎች ከበቂ በላይ… Read more: “ንገሩዋቸው፣ ምከሩዋቸው” ሌላ ጦርነት እብደት
- የባህር ወንበዴ ሲሳዮች – በገሃነም የሚመሰለው ስቃይየ34 ዓመቱ ኢትዮጵያዊ ከአውሮፕላኑ ሲወርድ እግሮቹ ቆስለው መራመድም ሆነ መቆም አቅተውታል። ብርክ ይዞት ይንገዳገዳል፡፡… Read more: የባህር ወንበዴ ሲሳዮች – በገሃነም የሚመሰለው ስቃይ
- ትህነግ ለአራተኛ ጊዜ የአማራ ህዝብ ላይ ወረራ በመፈጸሙ አማራ ክልል ህዝቡን ለመከላከል እንደሚገደድ አስታወቀ፤ ፌደራል መንግስት ጥያቄ ቀርቦለታል“ህወሓትና የግብረ አበሮቹ ፖለቲካዊ ግልሙትና እና ደም አፋሳሽ ጦርነት ለማድረግ ከመሞከር እንዲታቀቡ ይገባል” ሲል… Read more: ትህነግ ለአራተኛ ጊዜ የአማራ ህዝብ ላይ ወረራ በመፈጸሙ አማራ ክልል ህዝቡን ለመከላከል እንደሚገደድ አስታወቀ፤ ፌደራል መንግስት ጥያቄ ቀርቦለታል
- የራያ አላማጣ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሞላ ደርበው ሲገደሉ ሌሎች ሃላፊዎች ሸሽተዋል፣ ግድያውን ማን ፈጸመው?የራያ አላማጣ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሞላ ደርበው መገደላቸውን እና ሌሎች የወረዳው እና የከተማዋ… Read more: የራያ አላማጣ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሞላ ደርበው ሲገደሉ ሌሎች ሃላፊዎች ሸሽተዋል፣ ግድያውን ማን ፈጸመው?