አሸባሪው የሕወሓት ቡድን በአማራና በአፋር ክልሎች በወረራ ገብቶ የፈጸማቸውን አሰቃቂና ዘግናኝ የወንጀል ድርጊቶችን የሚያጣራ ግብረ ኃይል ተዋቅሮ ሥራ መጀመሩን የፍትህ ሚኒስቴር ገለጸ።
በሚኒስቴሩ ፕሬስ ሴክሬታሪ ዳይሬክተር አቶ አወል ሡልጣን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የሽብር ቡድኑ በለቀቃቸውና በወረራ ገብቶባቸው በነበሩ የአፋርና የአማራ ክልሎች ተንቀሳቅሶ የሚሠራ ግብረ ኃይል ተዋቅሮ የምርመራ ሥራ እየሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
ደረጃውን የጠበቀ፣ ገለልተኛና የወንጀል ድርጊቱን ይዘትና ስፋት ሊያሳይ የሚችል ዐቃቤ ሕጎችና ፖሊሶች በተለቀቁ አካባቢዎች ተገኝተው ምርመራ እያደረጉ ይገኛሉ፤ ከወንጀል ድርጊቱ ጋር በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ግንኙነት ያላቸውን ለማስረጃነት የሚጠቅሙ ግብአቶችን በማሰባሰብ ሰፊ የምርመራ ሥራ በማከናወን ላይ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።
እንደርሳቸው ገለጻ፤ ከፌዴራል ፖሊስና ከክልሎቹ የፍትህ ተቋማት ጋር የተቀናጀው የምርመራ ቡድኑ በጋራ ምርመራውን እያከናወነ የሚገኘው በደቡብ ወሎና በሰሜን ወሎ አካባቢዎች፣ በአፋር የተወሰኑ ወረዳዎች ላይ በመገኘት ነው።
አንዳንዶቹ ወንጀሎች ዓለም አቀፍ ወንጀሎች የሆኑ፣ በዓለም አቀፍ የወንጀል ፍርድ ቤት የሚቀርቡና ዓለም አቀፍ ድንጋጌን የጣሱ፤ የዘር ጭፍጨፋ፣ በሰዎች ላይ የሚፈጸሙ የወንጀል ድርጊቶች በመሆናቸው ምርመራው ዓለም አቀፍ መሥፈርትን ያሟላ እንዲሆን መደረጉን ተናግረዋል።
ምርመራው ዓለም አቀፍ መሥፈርትን ማሟላቱ ወንጀለኞቹ በየትም አካባቢ ቢገኙም ለማስቀጣት በሚያስችል ሁኔታ የማስረጃ ማሰባሰብ ሥራ እንዲሠራ የሚያስችል እንደሆነም ተናግረዋል።
የሽብር ቡድኑ በአፋርና አማራ ክልሎች የተለያዩ ከተሞችና ወረዳዎች በወረራ በመግባት ከፍተኛ ሰብአዊና ቁሳዊ ውድመት ሲያደርስ መቆየቱን አስታውሰው፤ ሰዎች ከአካባቢያቸው እንዲፈናቀሉ ምክንያት መሆኑንና አሰቃቂ ወንጀሎችን ሲፈጽም መቆየቱንም አመልክተዋል።
ከወታደራዊ እንቅስቃሴ ውጪ የሆኑ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ጭምር ኢላማ በማድረግ ጥቃት ሲፈጽም እንደነበረ፤ ያስታወሱት አቶ አወል አሸባሪ ቡድኑ በዓለም አቀፍ ሕግ ከተከለከሉ ተግባራት መካከል ንጹሃንን፣ ዩኒቨርሲቲዎች፣ ሆስፒታሎችን እንዲሁም ሰላማዊ ሰዎች የሚገለገሉባቸውን ተቋማት ጨምሮ የጥቃት ኢላማ አድርጎ ሲንቀሳቀስ መቆየቱን አስታውሰዋል።
አሸባሪ ኃይሉ የመከላከያ ሠራዊት ከትግራይ ክልል ከመውጣቱ በፊትም በክልሉ ማይካድራን ጨምሮ በአማራ ክልል አጎራባች ወረዳዎች በርካታ ወንጀሎችን ሲፈጽም ነበር። በእነዚህ ቦታዎች የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽንና የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብት ከፍተኛ ኮሚሽን የተውጣጡ ባለሙያዎች በቦታው ተገኝተው የሰብአዊ መብት ጥሰቱን ምርመራ ሲያከናውኑ መቆየታቸውን ተናግረዋል።
በዘላለም ግዛው
አዲስ ዘመን ታህሳስ 17 ቀን 2014 ዓ.ም
- Somaliland offended by G7 referring the Republic of Somaliland as “Somaliland Region of Somalia” The Republic of Somaliland, is a sovereign state with its own laws and… Read more: Somaliland offended by G7 referring the Republic of Somaliland as “Somaliland Region of Somalia”
- ” በትጥቅ ትግል ውስጥ ያሉ ወገኖቻችን አሁንም ሳይመሽ ቶሎ ወደ ድርድሩ እንዲገቡ በትህትና እንጠይቃለን ” ፕ/ር መስፍን አርአያየኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በሌላ መንገድ እየታገሉ ይገኛሉ ያላቸው አካላት ወደ ምክክር መድረኩ… Read more: ” በትጥቅ ትግል ውስጥ ያሉ ወገኖቻችን አሁንም ሳይመሽ ቶሎ ወደ ድርድሩ እንዲገቡ በትህትና እንጠይቃለን ” ፕ/ር መስፍን አርአያ
- የቡድን ሰባት አገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በኢትዮጵያ ጉዳይ የይሁንታና የስጋት ቅልቅል መግለጫ ሰጡየቡድን ሰባት ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በተለያዩ ጉዳዮች ላይ መግለጫ ሲሰጡ እግረመንገዳቸውን ኢትዮጵያን… Read more: የቡድን ሰባት አገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በኢትዮጵያ ጉዳይ የይሁንታና የስጋት ቅልቅል መግለጫ ሰጡ
- Foreign firms’ local market involvement entails economic dynamismPermitting foreign firm’s involvement in the import, wholesale and retail business, which was… Read more: Foreign firms’ local market involvement entails economic dynamism
- መንግስት የፕሪቶሪያው ስምምነት መጣስና የአማራን፣ትግራይና አፋር ህዝብን ማህበራዊ ዕረፍት መንሳት ተቀባይነት የለውም ሲል አስጠነቀቀMore stories የባህር በር ህልውና!!November 24, 2021 በደብረ ኤልያስ ‘የዓለም ብርሃን’ የተሰኘ አዲስ… Read more: መንግስት የፕሪቶሪያው ስምምነት መጣስና የአማራን፣ትግራይና አፋር ህዝብን ማህበራዊ ዕረፍት መንሳት ተቀባይነት የለውም ሲል አስጠነቀቀ
- ኢዜማ የብርን የመግዛት አቅም ማዳከም የኢኮኖሚውን ስብራት እንደማይጠግን አስታወቀመንግስት ከዓለም ዓቀፉ የገንዘብ ድርጅት ጋር ውይይት ላይ መሆኑ መጠቀሱን ተከትሎ ኢዜማ ”… Read more: ኢዜማ የብርን የመግዛት አቅም ማዳከም የኢኮኖሚውን ስብራት እንደማይጠግን አስታወቀ
- ዓለም ባንክና መንግስት በአሜሪካ እየመከሩ ነው፤ “የብርን የመግዛት አቅምንአዳክሙ” ጥያቄ ተቀባይነት ያገኛል?ዓለም ባንክና የዓለም ዓቀፉ የገንዘብ ተቋም ኢትዮጵያ የጠቀችውን ብድር ለመፍቀድ ያቀረቡት ዋና ቅድመ… Read more: ዓለም ባንክና መንግስት በአሜሪካ እየመከሩ ነው፤ “የብርን የመግዛት አቅምንአዳክሙ” ጥያቄ ተቀባይነት ያገኛል?
- የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነትና ወሰን አስመላሽ ኮሚቴ ለትግራይ ሕዝብ ጥሪ አቀረበ፤ “አማራ ልዩነትህን ወደጎን አድርግ፤ዳግም በጅምላ አንቀበርም”“የትግል አደራ አይታጠፍም፤ ዳግም በጅምላ አንገደልም!” በሚል ርዕስ የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነትና ወሰን… Read more: የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነትና ወሰን አስመላሽ ኮሚቴ ለትግራይ ሕዝብ ጥሪ አቀረበ፤ “አማራ ልዩነትህን ወደጎን አድርግ፤ዳግም በጅምላ አንቀበርም”