“ከድል በኋላ ያሉ ድኅረ ድል መዛነፎችን ማረም እና የጋራ መግባባት መፍጠር አስፈላጊ ነው” አቶ ተመሥገን ጥሩነህ

“ከድል በኋላ ያሉ ድኅረ ድል መዛነፎችን ማረም እና የጋራ መግባባት መፍጠር አስፈላጊ ነው” አቶ ተመሥገን ጥሩነህ

የአማራ ክልል ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች የምክክር መድረክ በባሕር ዳር እየተካሄደ ነው፡፡

የምክክር መድረኩ ዓላማ የክልሉን አመራር ለቀጣይ ተልዕኮ ማዘጋጀት እና ማብቃት ነው ተብሏል፡፡

የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል አቶ ተመሥገን ጥሩነህ ኢትዮጵያ የገጠማትን የሕልውና ጦርነት በተሟላ ድል የምታጠናቅቀው አፍራሽ አስተሳሰቦች ፈጽመው ሲከስሙ ነው ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ የገጠማት ጦርነት ወታደራዊ፣ ዲፕሎማሲያዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ትርጉም ያለው ዘርፈ ብዙ ነበር ያሉት አቶ ተመሥገን አንጸባራቂ ድሎች ተመዝግበዋል፤ ድሉም የመላው ኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ድል ነው ብለዋል፡፡

አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን በአማራ እና አፋር ክልል ወረራ ሲፈጽም የሀገሪቱን መውጫ እና መግቢያ በሮች በመቆጣጠር ኅልውናዋን መገዳደርና ወደሚፈልገው ድርድር መምጣት፣ በሱዳን በኩል መውጫ ኮሪደር ማስከፈት፣ የአማራን ሕዝብ አንገት ማስደፋት እና ኢትዮጵያን ማፍረስ ነበር ያሉት አቶ ተመሥገን የሽብር ቡድኑ በሁሉም ዘርፎች አልተሳካለትም ብለዋል፡፡

ከድል በኋላ ባሉ የድኅረ ድል መዛነፎችን ማረም እና የጋራ መግባባት መፍጠር ያስፈልጋል ያሉት አቶ ተመሥገን በችግሮች ላይ ሰፊ፣ ቀና እና በተግባር የተደገፈ ውይይት ከተደረገ መፍትሔዎቹ ቀላል ናቸው ሲሉ ገልጸዋል፡፡

በተጨማሪም በጦርነቱ የደረሰው ጉዳት ቀላል ባለመሆኑ የጋራ ትብብር እና ሕዝባዊ ተሳትፎ ወሳኝ ነው፤ የምክክር መድረኩም በዚህ ላይ ትኩረት ያደርጋል ነው ያሉት፡፡

ክልሉ ለወራት በዘለቀው ወረራ ማኅበራዊ፣ ምጣኔ ሃብታዊ እና ፖለቲካዊ መዛነፎች ተፈጥረዋል ያሉት የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ.ር) ከዚህ ዘርፈ ብዙ ፈተና በፍጥነት ለመውጣት ወጥ አቋም ያለው፣ በቆራጥነት የሚሠራ እና ሕዝብን የሚያገለግል የአመራር ሥርዓት መዘርጋት ጊዜ የማይሰጠው ጉዳይ ነው ብለዋል፡፡

ከችግሮቻችን በፍጥነት ለመውጣት ተከታታይ ምክክር፣ ውይይት እና ስልጠና ያስፈልጋል ያሉት ርእሰ መሥተዳድሩ የጋራ አቋም፣ ወጥ እሳቤ እና ተቀራራቢ አፈፃፀም አሁን ካለው አመራር የሚጠበቅ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በየደረጃው የሚገኘው የክልሉ ሕዝብ ሥራ አስፈፃሚ ከሕዝቡ ጋር መነጋገር፣ የጋራ መግባባት ላይ መድረስ እና በተግባር የተገለጸ ችግር ፈች እርምጃ ያስፈልጋል ያሉት ርእሰ መሥተዳደር ዶክተር ይልቃል ይህንን ለማድረግ ደግሞ በቂ ጊዜ ስለማይኖር ቀን እና ሌሊት ያለረፍት መሥራት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

See also  አሸባሪው ህወሓትን ለመደምሰስ በማንኛው መልኩ ዝግጁ መሆናችውን ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች አስታወቁ

ርእሰ መሥተዳድሩ መሰረታዊ የሆኑ የክልሉ ሕዝብ ጥያቄዎች እንዲመለሱ ቁርጠኛ አቋም መውሰድ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል፡፡ የምክክር መድረኩ ተሳታፊዎች የቀጣይ ተልዕኮ በዚህ “የጊዜ የለንም መንፈስ” የተቃኘ ሆኖ እንዲወጣም አሳስበዋል፡፡

በምክክር መድረኩ ከፌደራል እስከ ወረዳ ያሉ ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች ተሳታፊ ናቸው፡፡ ምክክሩም ለሦስት ተከታታይ ቀናት እንደሚቀጥልም ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ዘጋቢ፡- ታዘብ አራጋው – (አሚኮ)

  • “ደብረ ኤሊያስ ገዳም የደረሰበት ጉዳት የለም” ወረዳው፤ መከላከያ ስራውን መጨረሱ ተሰማ
    አካባባዊ በተለይም ገዳሙ ወታደራዊ ማስለጠኛ፣ የሚፈለጉ ሰዎች መመሸጊያ፣ ሃይማኖታዊ ዓላማውን የሳተ በመሆኑ በአባቶች፣ በሃይማኖት መሪዎች፣ በመንግስት ሃላፊዎችና ታውቃ ሰዎች ቢለመኑም ፈቃደኛ እንዳልሆኑ፣ በስተመጨረሻም ደብሩም ሆነ መኖኮሳቶች ምንም ሳይሆኑ መከላከያ ገብቶ ስራውን አከናውኖ መጨረሱ ተሰማ። በርካታ ታጣቂዎች ለመከላከያ እጃቸውን መስጠታቸውም ተገልጿል። ወረዳው መከላከያ ስራውን ጉዳት ሳያደርስ ማከናወኑን ይፋ ሲያደርግ እጅቻውን ስለሰጡናContinue Reading
  • አሮጌውን ወይን በአዲስ አቁማዳ ! የኖርንበት ፣ የቸከ የሰለቸ የፖለቲካ …
    የኢትዮጵያ ታሪክ የእርስ በእርስ ጦርነት civil war & strife ነው። ይሄንን ያደፈ ጉድለታችንን ማስተካከል የምንችለው መሀከለኛውን መንገድ የያዙ ስብስቦችን በማብዛት ነው። ችግሩ በእኛ ሀገር ፖለቲካ መሀከሉን መንገድ ልትይዝ ስትሞክር የሚወረወርብህ ፍላጻ መብዛቱ ነው። ለዚህ ጥሩ ምሳሌ ኢዜማ ነው። ህወሃትም ፣ የኦሮሞ ብሄረተኜችም ፣ በቅርብ የተፈለፈሉት የአማራ ብሄረተኞችም ለፓርቲው ያላቸውን ጥላቻContinue Reading
  • US Special Envoy for HoA Amb Mike Hammer to Visit Ethiopia
     US Special Envoy for the Horn of Africa Ambassador Mike Hammer will visit Ethiopia on May 31 – June 6. In Ethiopia, Ambassador Hammer will meet African Union officials on implementation of the November 2, 2022 Cessation of Hostilities Agreement (COHA). He will discuss progress and priorities including transitional justiceContinue Reading
  • በሽብር ወንጀል በተጠረጠሩ በ38 ግለሰቦች ላይ ተጨማሪ የ14 ቀን ጊዜ ተፈቀደ
    የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት በ3 መዝገብ የቀረቡ የ38 ተጠርጣሪዎችን ጉዳይ ተመልክቷል። ተጠርጣሪዎቹን ፍርድ ቤት ያቀረበው የፌደራል ፖሊስ መርማሪ በቀዳሚነት በነመላክ ምሳሌ መንግስቱ መዝገብ የተካተቱ 16 ግለሰቦችን እና በነደበበ በሻህ ውረድ መዝገብ የተካተቱ በ12 ተጠርጣሪዎች አጠቃላይ 26 ግለሰቦች ላይ የሽብር ወንጀል የጥርጣሬ መነሻውን በፅሁፍም በቃልምContinue Reading
  • ሟችን በጭፈራ የሚሸኘው ማህበረሰን
    በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በኮንሶ ዞን ውስጥ ተወልደው ያደጉት ዶ/ር ኦንጋዬ ኦዳታ በቅርቡ ነው አያታቸውን በሞት ያጡት። የሚወዷቸው አያታቸው ቀብር የተፈፀመው ግን ወዳጅ ዘመድ ተሰብስቦ ዘፍኖ እና ጨፍሮ በተከናወነ ሥነ ሥርዓነት መሆኑን ከቢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል። ሞት በሁሉም ዘንድ ሁሌም አዲስ ነው። በመጣ ቁጥር የሚያስደነግጥ በብዙ ማኅበረሰቦች ዘንድም ማቅ የሚያስለብስContinue Reading

Leave a Reply