እንቡዝ ሰው የሚሠራውንና የሚናገረውን በጤነኛ አእምሮ መረዳት አይቻልም። ጤነኛ አእምሮ በተጠየቅ፣ በሞራል ሕግ፣ በመረጃ፣ በማስረጃ፣ በሐሳብ ሙግት፣ ወዘተ. ነው የሚረዳው። እንቡዝ ጋ ይህ ሁሉ የለም። መቅበዝበዝ፣ መስከርና ማበድ አንድ ላይ ሆነው የሚፈጥሩት ሰብእና ነው።
በገድለ ተክለ ሃይማኖት የምናገኘው ሞተለሚ የተባለው የዳሞት ንጉሥ ለ25 ዓመታት እንቡዝ ሆኖ መኖሩን ይነግረናል። እንቡዝ የሚለውን ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ሲተረጉሙት፦ በቁሙ ልቡ የጠፋ፣ የተነበዘ፣ ነባዛ፣ ንብዝ፣ ቅብዝብዝ፣ ሰካር፣ እብድ፡፡ ሰብእ እንቡዛን፡፡ ብእሲት እንብዝት፡፡ እንቡዛነ ልብ ወድንቅዋነ እዝን (ኢሳ፳፭፡ ፭፡፡ ፶፬፡ ፮፡፡ መጽ፡ ምስ) ይሉታል። “ቅብዝብዝ ሰካር፣ እብድ” በሚሉት ነው አለቃ ለመበየን የሞከሩት።
ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን ታሪክ በጻፉ ጊዜ ሁሉ “እንቡዝ” የሚለውን “Insane” ብለው ነው የሚተረጉሙት። ኦክስፎርድ የእንግሊዝኛ መዝገበ ቃላት “Insane” የሚለውን ሲፈታ “in a state of mind which prevents normal perception, behaviour, or social interaction; seriously mentally ill.”
ይላል።
ሞተለሚ እንቡዝ ከሆነ በኋላ ያደረገው ነገር ይሄንን ትርጉም ያጠናክረዋል። ሥራው ያገኘውን ሁሉ ማጥፋት ነበር። ዓለም ልትጠፋ የሚገባት፣ ነገር ግን በደካሞች ምክንያት ሳትጠፋ የቀረች ትመስለው ነበር።
እንቡዝን ለመግለጥ አለቃ ኪዳነ ወልድ የተጠቀሙባቸውን ቃላት መመርመር የተሻለ ነገሩን ያሳየናል። መቅበዝበዝ – የመንፈስ አለመረጋጋት ነው። ይሄንን መጀመሪያ የተጠቀመው ቃየል ነው። ቃየል ወንድሙን በግፍ ከገደለ በኋላ መንፈሱ ያልተረጋጋ በመሆኑ ቅብዝብዝ ነበር። ወያኔም ገና ከጅምሩ መንገዱ የቃየል ነበር። ሰካር የአእምሮ መናወዝ ነው። በተጠጣ አስካሪ ነገር የሚመጣ ነው። ወያኔ ጎሰኝነት የሚባል አስካሪ መጠጥ ወስዷል። እብደት የልቡና መናወጽ ነው። ሥነ ልቡናዊ በሽታ ነው።
እንቡዝ ሰው የሚሠራውንና የሚናገረውን በጤነኛ አእምሮ መረዳት አይቻልም። ጤነኛ አእምሮ በተጠየቅ፣ በሞራል ሕግ፣ በመረጃ፣ በማስረጃ፣ በሐሳብ ሙግት፣ ወዘተ. ነው የሚረዳው። እንቡዝ ጋ ይህ ሁሉ የለም። መቅበዝበዝ፣ መስከርና ማበድ አንድ ላይ ሆነው የሚፈጥሩት ሰብእና ነው።
ወያኔ እንቡዝ ስለሆነ ለጤነኛ ሰው የሚሰጡ ነገሮች አይስማሙትም። የሚናገረውና የሚሠራው ከሰብእና ውጭ የሆነው በንብዘቱ ምክንያት ነው። ለምን አደረገ? ብትሉ ንዴቱ እናንተን ያሳምማችኋል እንጂ ወያኔ አይሰማውም። ያንን ሁሉ ጥፋት ሠርቶ፣ ያንን ሁሉ ወጣት አስፈጅቶ ፈገግ ይላል። ለምን ቢሉ? እንቡዝሰ እንቡዝ ውእቱ። እንቡዝ ምን ብታደርጉት እንቡዝ ነው።
By Daniel kebret
- ሸኔ መከፈሉ ተሰማ፤ በሺዎች የሚቆጠሩ ታጣቂዎቹ እጅ እየሰጡ ነው፤ ተማራኪዎቹ ድርጅቱ መፈረካከሱን አስታወቀ“የህግ የበላይነት ለማስከበር እየተወሰደ ያለዉን እርምጃ መቋቋም የተሳናቸው በሺዎች የሚቆጠሩ የአሸባሪዉ ሸኔ አባላት ለመንግስት እጅ ሰጡ” ሲል የዘገቡት መገናኛዎች እንዳሉት ድርጅቱ ቁመናው ፈርሷል። በቅርቡ በታንዛንያ ለስምምነት ብዙ ርቀት ከተኬደና ከንግገሩ መልካም ዜና የተጠበቀ ባለበት ወቅት ስምምነት ላይ እንዳልተደረሰ መንግስት ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። በሰላም ንግግሩ የተኩስ ማቆም ስምምነት ተደርሶ እንደነበር፣ አነጋጋሪ … Read moreContinue Reading
- ሰው ሰራሽ ቦይ በመገንባት ቀይ ባህርን መቀላቀል የኢትዮጵያ ሌላ አማራጭ?አርተፊሻል ቦይ በመገንባት ቀይ ባህርን ወደ ኢትዮጵያ በማምጣት ኢትዮጵያ የባህር በር ሊኖራት ይችላል፤ ይህ በአለም ላይ በኢትዮጵያ የአፋር ምድር ረባዳነት የተነሳ ተፈጥሮ የሰጠው እድል ነው! በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል አርተፊሻል ቦይ በመስራት ኢትዮጵያ የወደብ ባለቤት መሆን ትችላለች፡፡ እንደዚህ አይነት አጋጣሚ ሊፈጠር የቻለው፤ የኢትዮጵያ የአፋር ቦታ ከባህር ወለል በታች እስከ 110 … Read moreContinue Reading
- ብሄራዊ ባንክ የገንዘብ ቁጥጥሩን አጠንክሮ እንደሚገፋበት አስታወቀ፤ ህገወጥ የወርቅ አዘዋዋሪዎች ላይ እርምጃ እየተወሰደ ነው– የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አዲስ የማቋቋሚያ ረቂቅ አዋጅ አዘጋጀ በአገሪቱ የሚታየውን የዋጋ አለመረጋጋት ለመግራት የግንዘብ ስርጭት ላይ ጥብቅ ቁጥጥር በማድረግ የተጀመረው ስራ ውጤት እያሳየ መሆኑ ተመለከተ፤ ተጠናክሮ ክምሩ እንደሚሰራበትና ግሽበትን በዓመቱ መጨረሻ 20 ከመቶ ለማድረስ መታቀዱ ተሰማ። ህገወጥ የወርቅ ነጋዴዎች ላይ ጥብቅ ቁጥጥርና የማበረታቻ መደረጉ ለውጥ ቢያሳይም በቂ እንዳልሆነ ተመለከተ። … Read moreContinue Reading
- የኮሚሽኑ የቀድሞ ሠራተኞች ከ40 ሚሊየን ብር በላይ የሙስና ክስ ጋር ተያይዞ ያቀረቡት የክስ መቃወሚያ ውድቅ ሆነየአዲስ አበባ እሳት እና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የቀድሞ ሠራተኞች ከ40 ሚሊየን ብር በላይ የአልባሳት ግዢ ጋር ተያይዞ በቀረበባቸው የሙስና ወንጀል ክስ ያቀረቡት የክስ መቃወሚያ ውድቅ ተደረገ። ተከሳሾቹ ያቀረቡትን የክስ መቃወሚያ ውድቅ ያደረገው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው። የፍትሕ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ … Read moreContinue Reading
- መንግስት የነዳጅ ድጎማን በህገወጥ መንገድ ሲጠቀሙ ነበሩ ያላቸውን 40 ሺህ ተሽከርካሪዎች ከስርአቱ አስወጣ፣ የሰርቁትን ይከፍላሉየታለመለት የነዳጅ ድጎማን ላልተገባ ዓላማ ሲጠቀሙ የነበሩ 40 ሺህ ተሽከርካሪዎች ከድጎማ ስርዓቱ እንዲወጡና ዕዳ እንዲከፍሉ መደረጉን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዶክተር ፍጹም አሰፋ ገለጹ። ሚኒስትሯ ይህን ያሉት የመንግሥት የ2016 የመጀመሪያ የሩብ ዓመት አፈጻጸም በተገመገመበት ወቅት ነው። የግምገማው ተሳታፊዎች መንግሥት የነዳጅ ድጎማን ጨምሮ በርካታ የህዝብ ተጠቃሚነትን የሚያረጋገጡ ተግባራትን ማከናወኑን አድንቀው፤ ሆኖም” ድጎማው … Read moreContinue Reading
- በዓመት አምስት ሚሊዮን ቶን ሲሚንቶ የሚያመርተው ፋብሪካ ከመጋቢት በሁዋላ የሲሚንቶ ዋጋ ወደ ነበረበት የሚመልሰ ነውበቀን 10 ሺህ ቶን ሲሚንቶ እንዲያመርት እቅድ ተይዞለት በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን እንሳሮ ወረዳ ለሚ ከተማ እየተገነባ ያለውን የለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ የግንባታ በመጋቢት ወር ይጠናቀቃል። ምርቱ በተባለው ወር ሲጀምር የሲሚንቶ ዋጋ አሁን ካለበት በግማሽ እንደሚወርድ ይጠበቃል። ከመጋቢት በሁዋላ ፋብሪካው በ50 በመቶ የሲሚንቶ እጥረቱን ያስወግዳል። ኢስት አፍሪካን ሆልዲንግ ኩባንያ … Read moreContinue Reading
- አዲስ አበባ – ሙስና በገሃድ፤ የትራንስፖርት ፣ የመሬት፣ የካርታ፣ የግንባታ ፍቃድ ፣ የመታወቂያ … አገልግሎቶች ምሬት” የጸረ ሙስና ኮሚሽን ራሱ ሌላ መረማሪ ተቋም ሊበጅለት ይገባል” እስኪባል ድረስ ተቋሙ የነተበ ስለመሆኑ ያቋቋሙት አቶ መለስ በህይወት እያሉ የተሰጠ አስተያየት ነበር። ዛሬም ድረስ ያው ነው። ህዝብ በገሃድ የሚያየውን ሰላዮቹ “አልታየንም” ሲሉ የሚነከባከቡት ሌብነት ጉዳይ የብልጽግና ፈተና ሆኗል። በዚህ አያያዝ ፓርቲው ራሱን በራሱ ሊበላ እንደሚችል እየተጠቆመ ነው። በተቁማት ውስጥ … Read moreContinue Reading
- ህገወጥ የውጭ ገንዘብ አምራቾች ተያዙ፤ ማንነታቸውና ስማቸው መደበቁ ጥርጣሬ ፈጥሯልበኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሬ አጣቢዎችን ማንነት ለማወቅ ከባህር ማዶ ቢሮ ከፍተው ዶላር የሚሰበስቡትን ከመጠርሪያ ስማቸው በመነሳት መለያየት ቀላል ነው። በውጭ አገር ሆነው ፖለቲካ በመቀመርና ለፖለቲካ ቅመራው እርዳታ በመጠየቅ የዲጂታል ለማኝ የሆኑት ቢያንስ ይህን ስራ ቢሰሩ እንደሚሻላሸው ምክር የሚሰጡት ስራው እጅግ ከፍተኛ ገንዘው ወደ ሌላ አገር እያሻገረ በመሆኑ ነው። በዚሁ የምንዛሬ አጠባ … Read moreContinue Reading
- እጅግ ግዙፍ የበረዶ ግግር ተገምሶ ስፍራውን በመልቀቅ የሚያደርገው እንቅስቃሴ አስግቷልየለንደንን መጠነ-ሥፋት ከ2 እጥፍ በላይ የሚሆን የዓለማችን ትልቁ የበረዶ ግግር ተገምሶ እየሄደ ነው ተባለ፡፡ የበረዶ ግግሩ በፈረንጆቹ 1986 ላይ ከአንታርክቲክ ባሕር ዳርቻ ተቆርሶ በዌድል ባሕር አካባቢ የቆየ ሲሆን፥ ከመጠኑ ግዝፈት አንጻርም ‘የበረዶ ደሴት’ የሚል ስያሜን ይዞ በአካባቢው ከ30 አመታት በላይ ቆይታ አድርጓል። የበረዶ ግግሩ ‘የለንደን’ መጠነ ሥፋት ከሁለት እጥፍ በላይ … Read moreContinue Reading