“የሽብር ድርጊት በሚፈጠሩ አካላት ላይ የማያዳግም እርምጃ እንወስዳለን”

ክልሉን የትርምስ ቀጣና ለማድረግ የሽብር ድርጊት በሚፈጥሩ አካላት ላይ የማያዳግም እርምጃ እንደሚወሰድ የአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፋለ አስታወቁ፡፡
የአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፋለ በጎንደር ከተማ የተፈጠረውን ክስተት አስመልክቶ እንዳሉት፤ የክልሉ መንግሥት ተገቢውን ክትትል አድርጎ የማያዳግም እርምጃ ይወስዳል።
እንደ ሀገር ከገጠሙን ችግሮች ሙሉ በሙሉ ሳንላቀቅ ሃይማኖትን ምክንያት በማድረግ የእርስ በርስ ግጭት ለመፍጠር የሚጥሩ እኩይ አካላትን አንታገስም ብለዋል ርዕሰ መሥተዳድሩ።
ርእሰ መስተዳድሩ ክልሉን የትርምስ ቀጣና ለማድረግ የሽብር ድርጊት በሚፈጠሩ አካላት ላይ የማያዳግም እርምጃ እንወስዳለን ነው ያሉት፡፡
ይህ ሙከራ ኢትዮጵያን ካለችበት ነባራዊ ሁኔታ ለባሰ ቀውስ የሚዳርግ በመሆኑ ድርጊቱ ሊወገዝ ይገባዋል ነው ያሉት።
የክልሉ መንግሥት ተገቢውን ክትትል አድርጎ እርምጃ ይወስዳል ያሉት ርዕሰ መሥተዳድሩ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ወጣቶች ለሰላም ዘብ እንዲቆሙማሳሰባቸውን አሚኮ ዘግቧል፡፡
Related posts:
ባልደራስ የሱዳን ልሳን - የሱዳን የውስጥ ቀውስ ማስተንፈሻ ዜና ያራባል
በአፋር የተደበቁ 15 ነዳጅ የጫኑ ቦቴዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ
ኢራን እና አርጀንቲና “ብሪክስ”ን ለመቀላቀል ማመልከቻ አስገቡ
ብልጽግናና የቻይና ኮሚዩኒስት ፓርቲ ስትራቴጂካዊ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ተስማሙ
ከሶስት ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የባቡር የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማት የሰረቁ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ
ፖሊስ ጥፋተኞችን መቅጣቱንና የቆዩ ፊልሞች በፖሊስና ህዝብ መካከል ክፍተት ለመፍጠር እየተሰራጩ መሆኑንን ገለጸ
ከህወሓት ጋር የገጠመንን ግጭት በድርድር ለመፍታት የተጀመሩ ጥረቶች የሚደገፉ ናቸው
ከ12 ሺህ 400 በላይ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ገለጸ