የሩሲያ ጦር በምሥራቃዊ ዩክሬን ስልታዊ ጠቀሜታ አላት የተባለች ከተማ መኦቅጣጠሩ ትገለጸ። ፑቲን ዩክሬን በጥቁር ባህር ወደብ ጎተራዎቿ ያከማቸችውን እህል ወደ ሌለኦች አገራት መላክ በምትችልባቸው አማራጮች ላይ ለመነጋገር ፈቃደኛ መሆናቸውን አስታወቁ።
የሩሲያ ጦር በምሥራቃዊ ዩክሬን ዶንባስ ግዛት የምትገኘውን ሊማን የተባለች አነስተኛ ከተማ መቆጣጠሩን አረጋገጠ። የጦሩ ማረጋገጫ የተሰማው ከዩክሬን መገንጠልን የሚያቀነቅኑ የሩሲያ ደጋፊ ታጣቂዎች ስልታዊ ጠቀሜታ አላት የተባለችን ከተማ ትላንት አርብ እንደተቆጣጠሩ ከገለጹ በኋላ ነው። የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢጎር ኮናሼንኮቭ “በዶኔትስክ ሕዝቦች ሪፐብሊክ ኃይሎች እና በሩሲያ ጦር ጥምር እርምጃ የክራስኒ ሊማን ከተማ ከዩክሬን ብሔርተኞች ሙሉ በሙሉ ነጻ ወጥታለች” ብለዋል።የዩክሬን ጦር ከተማይቱን ተቆጣጥሮ ለመቆየት በተደረገ ውጊያ ከፍተኛ መሰናክል እንደገጠመው በዛሬው ዕለት ይፋ አድርጓል። የሊማን ከተማ ምሥራቃዊ ዩክሬንን ከደቡብ ምዕራብ የአገሪቱ ክፍል የሚያስተሳስሩ የባቡር እና የአውራ ጎዳና መሠረተ-ልማቶች የሚገኙባት በመሆኗ ስልታዊ ጠቀሜታዋ ከፍ ያለ ነው። ሩሲያ ከተማይቱን መቆጣጠሯ በዶንባስ ግዛት በዩክሬን ኃይሎች ቁጥጥር ሥር ወደሚገኙት የዶኔትስክ እና ሉሐንስክ ከተሞች ለመገስገስ አመቺ ሁኔታ እንደሚፈጥር አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል። በሉሐንስክ ግዛት በሚገኙ ሁለት ከተሞች ዛሬ ቅዳሜ ውጊያ እየተደረገ ይገኛል። የሩሲያ ኃይሎች በከበቧት የሲቪየርዶኔትስክ ከተማ ብቻ በጦርነቱ 1,500 ሰዎች መገደላቸውን የከተማዋ ከንቲባ ተናግረዋል። ከጦርነቱ በፊት የ100,000 ሰዎች መኖሪያ በነበረችው በዚችው ከተማ የቀሩት ከ12,000 እስከ 13,000 ገደማ ብቻ ሲሆኑ 90 በመቶ ሕንጻዎቿ መውደማቸውን አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል።
ፑቲን ዩክሬን እህል መላክ በምትችልባቸው አማራጮች ላይ ለመነጋገር ፈቃደኛ መሆናቸውን ገለጹ
ዩክሬን በጥቁር ባሕር ወደቦች በሚገኙ ጎተራዎች የተከማቸ እህል ወደ ሌሎች አገራት መላክ በምትችልባቸው አማራጮች ላይ ለመነጋገር ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን ፈቃደኛነታቸውን አሳዩ። ጽህፈት ቤታቸው ክሬምሊን ባወጣው መግለጫ እንዳለው ፑቲን ዛሬ ቅዳሜ ከጀርመኑ መራሔ-መንግሥት እና ከፈረንሳዩ ፕሬዝደንት ጋር ባደረጓቸው የስልክ ውይይቶች በጉዳዩ ላይ ለመነጋገር ፈቃደኛ መሆናቸውን አሳውቀዋል። የክሬምሊን መግለጫ “የዩክሬን እህል ከጥቁር ባህር ወደቦች ወደ ውጪ መላክን ጨምሮ እህል ያለገደብ ወደ ውጪ የሚላክባቸውን አማራጮች ለማግኘት ሩሲያ በበኩሏ ፈቃደኛ ነች” ብሏል። ሩሲያ የተጣሉባት ማዕቀቦች ከተነሱ ወደ ውጪ የምትልከውን የአፈር ማዳበሪያ እና የግብርና ምርቶች ለመጨመር ፈቃደኛ እንደሆነች ፑቲን ለጀርመኑ መራሔ-መንግሥት ኦላፍ ሾልዝ እና ለፈረንሳዩፕሬዝደንት ኤማኑዌል ማክሮ ተናግረዋል። ፑቲን ይኸንኑ ጉዳይ ከዚህ ቀደም ከጣልያን እና ከኦስትሪያ መሪዎች ጋር ባደረጉት ንግግር አንስተው ነበር። ዩክሬን እና ምዕራባውያን አገሮች ሩሲያ ዩክሬንን በመውረሯ የተፈጠረውን ዓለም አቀፍ የምግብ ቀውስ የፑቲን መንግሥት እንደመሣሪያ ተጠቅሟል ሲሉ ይወነጅላሉ። ከጦርነቱ በኋላ የእህል፣ የምግብ ማብሰያ ዘይት፣ የነዳጅ እና የማዳበሪያ ዋጋ አሻቅቧል። ፑቲን ምዕራባውያን አገራት ለዩክሬን የጦር መሳሪያ መላካቸውን መቀጠላቸው አደገኛ እንደሚሆን ሾልዝ እና ማክሮንን አስጠንቅቀዋል ተብሏል። በክሬምሊን መግለጫ መሠረት ፕሬዝዳንት ፑቲን የጦር መሳሪያ አቅርቦቱ ሁኔታውን የበለጠ የማያረጋጋ እንዲሁም ሰብዓዊ ቀውሱን የሚያባብስ እንደሚሆን ተናግረዋል። የሩሲያ ፕሬዝደንት ከዩክሬን ጋር የተቋረጠውን ድርድር እንደገና ለመጀመር ፈቃደኛ መሆናቸውን እንዳሳወቁ ክሬምሊን ገልጿል። DW
- Landlocked Ethiopia to Rebuild its NavyFrance agreed to support Ethiopia to build a naval force, yet it would take years for Ethiopia to procure the ships and train the forces required for… Read more: Landlocked Ethiopia to Rebuild its Navy
- Ethiopia and Eritrea Have a Common EnemyBy Bronwyn Bruton Ethiopia’s new prime minister, Abiy Ahmed, made headlines across the world with his surprise move last month to resolve his country’s two-decade-long fight with Eritrea. The nation of Eritrea… Read more: Ethiopia and Eritrea Have a Common Enemy
- The Ethiopian elections are an imperfect step in the right directionby Birtukan Midekssa June 20, 2021 on June 21, Ethiopians will go to the polls for the country’s sixth general elections More stories GERD’s Power Generation In Accordance… Read more: The Ethiopian elections are an imperfect step in the right direction
- Construction of 10 Bil Birr Worth Irrigation Dam Launched in OromiaThe construction of Anger Irrigation Dam with a cost of 10 billion Birr was launched on Sunday in Gida Ayana Woreda of East Welega Zone ,Oromia Regioan… Read more: Construction of 10 Bil Birr Worth Irrigation Dam Launched in Oromia