“ወልቃይት እንዴት እንደኖረ ያውቃል። ምን እንዳሳለፈ ይረዳል። ወልቃይት ውስጧ ምን ሲከናወን እንደነበር አትዘነጋም። ታዲያ ማን ወደዛ ዳግም ያያል? ማንስ ያ ዳግም እንዲመጣ ይፈቅዳል? የውልቃይት ቃል ኪዳኗና የጀግኖቿ ህብረት ለዳግም ቀንበር ዕድል አይሰጡም። ደፍሮ በክፉ ምኞት የሚመጣ ካለ ዋጋው የሚታውቀ ነው። ይህን በመረዳት ወደ ቀናው መንገድ መመለስ፣ ከጥፋትና በድለ መማር የተሻለ ይሆናል። ህዝብና ህዝብ መካከል የተገነባውን የተንኮል አጥርም ማፍረስ የሚቻለው በዚ መልኩ ነው” ከቀድሞ የክልሉ ነዋሪዎች የተወሰደ
ጀግና ጀግናን ያውቃል፤ ጀግናን ያከብራል፣ይወዳል፣ ያወድሳል፣ ይሸልማል። ጎበዝ ጎበዝን እየወለደ በማሳደግ ለወገን አለኝታ ለሀገርም ዘብ ይኾን ዘንድ ያበረክታል። ጀግና ሁልጊዜም ሀቀኛ ነው። የሰው አይመኝም የራሱንም አይሰጥም። መከራ ይበዛበት ይኾናል እንጅ አንገቱን ሊያስደፋው ግን አይቻለውም። ለጦር አይንበረከክም፣ ወሬም በፍፁም አይፈታውም! ይሄንን ሀቅ ወልቃይት ላይ አየን።
ወልቃይቴው የአማራ ሕዝብ የዘመን መቀያየር የሚወልደው ክፉ እሳቤ ይፈትነው ይኾናል እንጅ ከቶውንም ለሀገር ያለውን ፍቅር እንደማይቀንስበት አስመስክሯል። በኢትዮጵያዊነት ስም ተሸፋፍኖ በሕዝብ ጫንቃ ላይ ተጭኖ የቆየው አሸባሪው የትግራይ ቡድን በተለይም ለወልቃይቴ አማራዎች ከአርባ ዓመታትም የላቀ የመከራ ዘመንን አስመዝግቦ አልፏል። ይኽ ፅኑ እና የተራዘመ መከራ ወልቃይቴ አማራዎችን እንደወርቅ እየፈተነ የሀገር ፍቅራቸውን የበለጠ አበራላቸው እንጅ ከኢትዮጵያዊነት ማማ ማንሸራተት ግን አልተቻለውም።
የወልቃይቴዎች አማራዊ ማንነትና ኢትዮጵያዊ መንፈስ በትሕነግ የክፋት መዶሻ ቢወቀርም የበለጠ መገለጥ እንጅ አልደበዝዝ አለ። የሀገር ፍቅር ተምሳሌት ከዚህ ወዲያ ላሳር ነው። ለዚኽ ሁሉ ግፍ እጅ ሰጥቶ አንገት አለመድፋትም የጀግንነት መለኪያ ሚዛንነት ነው።
ሚዛኑ የወልቃይት አማራ ለትዕግስቱና ለፅናቱ ፍሬ የሚኾን የሱ ቀን መጣለት። የኾነው ኹሉ ኾኖ ነፃነቱን በእጁ አስገባ። ዛሬ ወልቃይት ለዘመናት የተነጠቀ ሀቁን ዞሮ ተቆናጠጠ። በአማራዊ ማንነቱና በኢትዮጵያዊ ክብሩ መኖር ጀመረ።
ጀግና ለሌላው ክብርና ሞገስን አይነፍግም። ዛሬ ጀግናው የወልቃይት ሕዝብ ጀግኖቹን ሲያወድስ ውሏል። ዞኑ ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ነው። ወረዳው ወልቃይት፤ በዋና ከተማዋ ወፍአርግፍ ከተማ በተዘጋጀ መድረክ የዞን ከፍተኛ አመራሮች፣ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ከፍተኛ የጦር አመራሮች እንዲኹም የአማራ ልዩ ኃይል ከፍተኛ አዛዦች ተገኝተው ከወልቃይት ሕዝብና ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች ምስጋና ቀርቦላቸዋል።
የመድረኩ ዋና ዓላማ የኢትዮጵያን ዳር ድንበር ለማስከበር ውድ ሕይወታቸውን የሚሰጡ የመከላከያ ሠራዊትና የልዩ ኃይል አባላትን ለማመስገንና ቀጣይ ደጀንነትን ለመግለፅ ነበር።
የወልቃይት የሀገር ሽማግሌዎች እና የሃይማኖት አባቶች በመድረኩ ተገኝተው የኢትዮጵያ ዘብ የሆኑትን የፀጥታ አካላት አመስግነዋል። “ወልቃይት ጠገዴን ብሎም መላውን ኢትዮጵያውያን ነፃ አውጥታችኋልና ክንዳችሁን አይቆርጥመው” ብለዋል።
የወልቃይት ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ክብረአብ ስማቸው ለጦር አመራሮች እንኳን ደኽና መጣችሁ በማለት የወልቃይት ሕዝብ በግንባርም ይሁን በደጀንነት በመሰለፉ ለድልና ለነፃነት መብቃትን ተናግረዋል። ሕዝቡ ከአማራ ልዩ ኃይልና ከመከላከያ ሠራዊት ጎን ለአፍታም የማይርቅና በተፈለገበት ግንባር ኹሉ ዝግጁ እንደኾነም አረጋግጠዋል።
የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሸተ ደምለው ወልቃይቴነት ከአርባ ዓመታት በላይ በዘለቀው የትህነግ ስቃይ ሸብረክ ያላለ ከብረት የጠነከረ አማራዊ ማንነት እንደሆነ ገልፀዋል። የወልቃይት ነፃነት እንዲመጣ ለተፋለሙ መላው የፀጥታ አካላትም ምስጋና ሰጥተዋል።
“ትሕነግ የቀረው ብቸኛው ጉልበቱ ውሸትና ማምታታት ስለሆነ መላ ኢትዮጵያውያን ነቅተው መታገል አለባቸው” ብለዋል። አሁን ላይ የተገኘው ድል ሙሉ በሙሉ እንዲረጋገጥ የዞኑ ሕዝብ ከመከላከያ ሠራዊትና ከልዩ ኃይል ጎን ከመቆም በተጨማሪ የትሕነግ ተላላኪዎችን በመለየት እየታገለ ነው ብለዋል። “የታፈረችና የተከበረች ሀገር ለመመስረት ጠንካራ መከላከያ አስፈላጊ ነው” ያሉት አቶ አሸተ ወጣቶች መከላከያ ሠራዊትን በተለያዩ ሙያዎች በመቀላቀል ለሀገር ዘብ መኾን አለባቸው ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሑመራ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የሰላምና ደኅንነት መምሪያ ኀላፊ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ በመድረኩ ተገኝተው ጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊትና የአማራ ልዩ ኃይል ከሌሎች ሰላም አስከባሪዎች ጋር በመቀናጀት ላስገኙት ነፃነት ምስጋና አቅርበዋል። የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ ከመከላከያ ጎን ቆሞ ሀገሩን ለመጠበቅ አስፈላጊውን ሁሉ የደጀንነት ሥራ ማከናወኑን ገልፀዋል።
የወልቃይት ሕዝብ ያዘጋጀውን የአካባቢውን ሙሉ ባሕላዊ አለባበስ የሚያሳዩ አልባሳትና ቁሳቁስንም ለጦር አመራሮች በክብር አልብሰዋል።
የጦር አመራሮች የወያኔ ጉልበቱ ጥይቱ ሳይኾን የሀሰት ፕሮፓጋንዳው ነው ብለዋል። “ጠላት ወልቃይት የገባ አስመስሎ የሚያሰራጨው መረጃ የሀሰት ፕሮፓጋንዳው አንዱ ማሳያ ነው” ያሉት የጦር አዛዥ ይህ ፍፁም ከእውነት የራቀ በመኾኑ ሕዝቡ መምታታት የለበትም ብለዋል። የትሕነግን ተከዜን ተሻግሮ ወልቃይት የመግባት ህልም ባዶ የሚያስቀር የሠራዊት አቅም ተገንብቷል ሲሉም ተናግረዋል።
የወልቃይት ሕዝብ ወያኔን አምርሮ ታግሏል፤ አሁንም ቢኾን ለመከላከያና ለልዩ ኃይል ያለው ደጀንነት የሚያኮራ ነው ብለዋል። አሸባሪው ትሕነግ ወልቃይትን ተቆጣጥሮ ከውጭ ጠላት ጋር በመገናኘት ሀገር የማፍረስ ዓላማን ይዞ ስለሚባዝን ሁሉም ኢትዮጵያዊ በአንድነት ቆሞ መታገል ይገባል ሲሉ ከፍተኛ ጦር አዛዦች መልዕክት አስተላልፈዋል።
ዘጋቢ:- አሚናዳብ አራጋው
- U.S Senator Robert Menendez, His Wife, and three businessmen charged with bribery offensesU.S. Attorney Damian Williams said: “As the grand jury charged, between 2018 and 2022, Senator Menendez and his wife engaged in a corrupt relationship with Wael Hana, Jose Uribe, and Fred Daibes – three New Jersey businessmen who collectively paid hundreds of thousands of dollars of bribes, including cash, gold, … Read moreContinue Reading
- Veteran Diplomat Ketema Yifru Awarded Bego Sew Special AwardIt was indicated during the ceremony that Ketema had also served his country in various responsibilities in addition to his contributions to the establishment of the Organization of African Unity and pan-Africanism. (ENA):- Veteran Diplomat Ketema Yifru has been awarded the 2023 Bego Sew special Award for his outstanding contribution … Read moreContinue Reading
- Why G20’s debt-relief strategy is failingThe Indian Prime Minister says a G20 strategy has driven global debt restructuring since his country assumed leadership. That’s not the full picture. By Biswajit Dhar – downtoearth.org.in Indian Prime Minister Narendra Modi, who is about to host G20 leaders in New Delhi, has boasted about his country’s role in easing global … Read moreContinue Reading
- G20 Summit: Good progress on easing debt in Zambia, Ethiopia & Ghana, says finance ministerIndia releases G20 New Delhi Leaders’ Declaration stating developing countries would need $5.8-5.9 trillion up to 2030 to implement Nationally Determined contributions By Rohini Krishnamurthy – downtoearth.org.in There has been good progress in helping address the debt situation in Zambia, Ethiopia and Ghana, Union Finance Minister (FM) Nirmala Sitharaman, said during a press … Read moreContinue Reading
- Netanyahu wants immediate deportation of Eritreans after Tel Aviv violenceIsrael is considering tough steps including the immediate deportation of Eritrean asylum seekers involved in riots in Tel Aviv on Saturday. By Yolande Knell – BBC News, Jerusalem Some 170 people were injured in violent clashes with police and in-fighting between groups of supporters and opponents of the Eritrean regime. … Read moreContinue Reading