የከተማችንን አሁናዊ ሁኔታ መነሻ በማድረግ የሰዓት እላፊ ገደብ በማውጣት የተለያዩ ክልከላዎችን ማስቀመጥ በማስፈለጉ የከተማ አስተዳደሩ የጸጥታ ምክር ቤት የሚከተሉትን ውሳኔዎች አስተላልፏል።
1) በከተማችን ከምሽቱ 2:00 እስከ ጧቱ 12:00 ድረስ ማንኛውም የሰውና የተሽከርካሪ ከቦታ ቦታ ማንቀሳቀስ የተከለከለ ነው ::
2) ለግዳጅ የሚፈለጉ ተሽከርካሪዎችን አለመተባበር እና የተለያዩ ምክኒያቶችን በመደርደር ፍላጎት አለማሳደር በፍፁም የተከለከለ ነው::
3) ከምሽቱ 2:00 ሰዓት ጀምሮ ማንኛውም መጠጥ ቤቶች ምግብ ቤቶች የሻሂ ቤቶችና፣ ሆቴሎች ፣ ከተፈቀደለት ስአት ውጭ ቤት ከፍቶ ማስተናገድ የተከለከለ ነው::
4) ፀጉረ ልውጥ ሰዎችን ማሳደር ወይንም ለሚመለከተው ህግ አስከባሪ አካል ጥቆማ ሰጥቶ አለማሰያዝ የተከለከለ ነው ::
5) ማንኛውም የከተማችን ወጣቶች ለወገን ጦር እውነተኛ የኋላ ደጀን የመሆን ሎጀስቲክ እና ተተኳሺ የማቅረብ ግዴታ ዛሬ ስለአለበት ፣ ቆቦ ከተማ የሚገኝ ወጣት በሙሉ ቆቦ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ጽ/ቤት እየተገኛቹሁ ተመዝገቡ ፣
6) በማንኛውም የከተማችን ቤትና የንግድ ቤት ቁማር / ቢንጎ ; ካርታ ; / መጫወት ማጫወት ; የመጫወቻ ቦታ ማከራየት ; በፍጹም የተከለከለ ነው ::
7) በከተማችን ሁሉም የሚገኙ የመንግስት ተቋማት የሚገኙ የመንግስት ሰራተኞች እና የቀበሌ መዋቅር ከመቸውም ግዜ በበለጠ ሁኔታ ለህብረተሰቡ ተደራሺ የሆነ ሙያዊና መንግስታዊ ሃላፊነቱን የመወጣት ግዴታ አለበት::
8)ባጃጂና ወደ ባጃጂ ማህበር አባል ያልገባ
ባጃጂ መንቀሳቀስ አይቻልም ::
9) ሆርን ኦፍ አፍሪካ ኤፍ ኤም 88.0 አሁን ላይ ስርጭት ስለጀመረ ከጧቱ 1:00-3:00 ቀን ከ6:00-80:00 ማታ ከ10:00- 12:00 በአማርኛ ; በትግርኛ ; ስለሚተላለፍ ትከታተሉ ዘንድ እናሳውቃለን ::
10) የሸቀጥ እቃወችን / ክብሪት ; ዳቦ እርሾ ; መድሀኒት ; ዘይት ; ስኳር; አረቂ ወዘተ/ ቦታ ማንቀሳቀስ ; ህገ ወጥ የገንዘብ ዝውውር ; ህገ-ወጥ ንግድ የተሳተፈ አካል በህግ ይጠየቃል ::
11)በከተማ አስተዳደሩ ጥይት የተኮሰ ያስተኮስ በተቀመጠው ውሳኔ መሰረት በህግ ይጠየቃል
12) በህዝብ መዝናኛ ቦታወች ; በገበያ ማእከል ; በሀይማኖት ተቋማት ; በሆቴልና ካፌ በመሳሰሉት ቦታወች ላይ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ የተከለከለ ነው ::
ይህ ክልከላ አሸባረውን የትግራይ ወራሪ ሃይልን ቀብረን አማራን ከውርደት ኢትዬጲያንም ከብተና ለመታደግ የሚደረገው ትግል እስከሚጠናቀቅ ድረስ ፀንቶ የሚቆይ ይሆናል:: ይህንን ውሳኔ የማያከበር ግለሰብም ሆነ ድርጅት ላይ የፀጥታ መዋቅሩ አስፈላጊውን የእርምት እርምጃ የሚወስድ መሆኑን ጭምር በአጽእኖት እያሳወቀን ለክልከላው ተግባራዊነት ሁላችንም የበኩላችንን እንድንወጣ እናሳስባለን፡፡ ::
የቆቦ ከተማ አስተዳደር ፀጥታ ም/ቤት
05/02/2015
በቆቦ ከተማ