ህገወጥ የኤሌክትሪክ ቆጣሪ ለመግጠም የሞከሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ

አዲስ የኤሌክትሪክ ቆጣሪ እንገጥመላችኋለን በማለት ህገ ወጥ የኤሌክትሪክ ቆጣሪ ይዘው የተገኙ ተጠርጣሪዎች እጅ ከፍንጅ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የኦሮሚያ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት አሳውቋል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ ጥቅምት 30 ቀን 2015 ዓ.ም አንድ የሞጆ ከተማ ነዋሪ የሆነ ግለሰብ በላ ሶስት ፌዝ ቆጣሪ እንገጥምለሃለን በማለት አታለው ገንዘብ ቢቀበሉትም፤ ግለሰቡ ሁኔታውን ተጠራጥሮ በአቅራቢያው ለሚገኘውን የሞጆ አገልግሎት መስጫ ማዕከል ጥቆማ መስጠቱን ተገልጿል፡፡

ማዕከሉም ጉዳዩን ለአካባቢው ፖሊስ በመጠቆም ተጠርጣሪዎቹ ከያዙት ቆጣሪ ጋር እጅ ከፍንጅ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡

መሰል እኩይ ተግባራትና ማጭበርበሮች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣ ሲሆን፤ ክቡራን ደንበኞቻችንም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልገሎት ብቸኛና ህጋዊ የኤሌክትሪክ ቆጣሪ አቅራቢ መሆኑን አውቃችሁ ከደላሎችና ከአጭበርባሪዎች ራሳችሁን እንድትጠብቁ ሲል አገልግሎቱ ጥሪ አቅርቧል፡፡

(ኢ.ፕ.ድ)

See also  መከላከያ በጃዊ የጥፋት ሃይሎች ሴራ አከሸፈ፤ ታጣቂዎቹ ትጥቅ ለመፍታት ተስማሙ

Leave a Reply