ተንቀሳቃሽ ንብረትን ዋስትና በማስያዝ የብድር አገልግሎት ማግኘት የሚያስችለው አዋጅ በቅርቡ ይፋ ይደረጋል

ተንቀሳቃሽ ንብረትን ዋስትና በማስያዝ የብድር አገልግሎት ማግኘት የሚያስችለው አዋጅ በቅርቡ ይፋ እንደሚደረግ የብሔራዊ ባንክ ገዢ ዶክተር ይናገር ደሴ ገለጹ።

በኢትዮጵያ ካሉት ዜጎች  አንጻር ብድር የወሰዱ ዜጎች እጅግ አነስተኛ መሆናቸውንም የሚያነሱት ገዢው በሀገሪቱ ውስጥ ከሚገኙ ባንኮች እስካአሁን ከ330ሺ ለማይበልጡ ስዎች ብቻ ብድር መስጠታቸውን ገልጸዋል። በአንጻሩ የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ከ6 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ብድር መስጠታቸውን ነው ያነሱት።

አሁን ላይ ይህን ችግር ለመፍታት ተንቀሳቃሽ ንብረትን በዋስትና በማስያዝ የብድር አገልግሎት የሚሰጥበት አዋጅን ተግባራዊ ለማድረግ ዝግጅት መጠናቀቁን ነው የጠቆሙት። በዚህም በተለይ አርብቶ አደሩ እና አርሶ አደሩ እንስሳትን፣ ግመሎችን ፣ የግል ደኖችን፣ የመሬት መጠቀሚያ ደብተሮችን እና የመሬት መብትን በማስያዝ እና በሌሎችም ብድር ማግኘት የሚችል መሆኑን ነው ያነሱት።

ይህ አዋጅም በቅርቡ በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ ይፋ እንደሚደረግምና ይህ አዋጅም ምርትና ምርታማነትን ከማሳደግ አንጻር ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው መሆኑንም ተናግረዋል። በየአካባቢው የሚገኙ የባንክ ቅርንጫፎችና የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማትም ዝግጅት  እየተደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል ሲል የዘገበው ኢዜአ ነው።

See also  ሎጀስቲክስ መምሪያ - የጀርባ አጥንት!!

1 Comment

  1. Your article gave me a lot of inspiration, I hope you can explain your point of view in more detail, because I have some doubts, thank you.

Leave a Reply