ጉድ ሳይሰማ መስከረም አይጠባም !

እኚ እናት ወ/ሮ ዘንባቤ ጫላ ይባላሉ ። ለበርካታ አመታት በመድኃኒት ፋብሪካ በመስራት ባጠራቀሙት ገንዘብ ከ11 አመት በፊት ቤት ሰርተው ትዳር መስርተው ይኖሩ ነበር ። ሆኖም ትዳራቸው ሰምሮ ከአጋራቸው ጋር አብሮ ለመኖር ልጅ መውለድ ባለመቻላቸው ምክንያት እና ባል ከሌላ ለሚወለዱ ልጆቹ ከጀርባ በኩል ያለው ቤት ይሰጣቸው በሚል አለመግባባት ወደ ፍቺ ያመራሉ ። ባል ያለፋበትን ፣ ያልደከመበትን እሳቸው ዘመናቸውን ሙሉ የደከሙበትን ከትዳር በፊት የሰሩትን ንብረት ይገባኛል ፤ ሲል ፍርድ ቤት ከሶ የድርሻውን በመውሰድ ቀሪውን ደግሞ በጉርብትና አልኖርም በማለት ወይዘሮ ዘንባቤ ሸጠው ሁለት የተለያዩ ቦታዎች ላይ ቤት በመግዛት አንዱን በማከራየት በክራዩ ገቢ ኑሮቸውን ይደጉሙ ጀመር ።

ከለታት አንድ ቀን በሀይማኖት ከሚመስሎቸው ጓደኛቸው አንድ ሀሳብ መጣ ። ይህው “ቤት ውስጥ ብቻዎትን ከሚኖሩ ከጎን ያለችውን ሶስት በአራት የሆነችውን ክፍል ለምን አከራይተው አንድም ገቢ ያገኛሉ ሁለትም የሚያናግሮት ፣ የሚጫውቶት ሰው ያገኛሉ ። ” ትልና ሀሳብ ታቀርባለች ። እውነት ነው ። ብለው በጓደኛቸው ሀሳብ የተስማሙት ወ/ሮ ዘንባቤ ተከራይ አግኝቼልሻለሁ በማለት ሀሳቡን ያቀረቡ ጓደኛቸው በቸርች የምታውቃትን ሴት እንድትከራይ ያደርጋሉ ።

ወ/ሮ ዘንባቤ ቸርች በመሄድ የአምልኮ ስርዓት ይፈፅሙ የነበረ ቢሆንም ተከራይታ የገባችው ሴት እኔ አገልጋይ ነኝ በማለት ቤት ውስጥ ታገለግላቸው ጀመረ ። ትፀልይላቸዋለች ፣ መልዕክት ታመጣላቸዋለች ፣ ዘይት ትቀባቸዋለች ፣ ትንቢት ትተነብይላቸው ጀመረ ። ወይዘሮ ዘንባቤ ሁሉን እውነት ብለው በመቀበል ቸርች መሄድን እርግፍ አድርገው በመተው በቤታቸው የሚሆነውን ነገር ለቤተሰቦቻቸው ሳያማክሩ ይቀጥላሉ ።

ወይዘሮ ዘንባቤ ከለታት በአንዱ ቀን እንዲህ ሲሉ ለምትፀልይላቸው ተከራያቸው ውስጣቸው ያለውን ሚስጥር ያካፍላሉ ። ” ስሞት እሩቡን ለቤተክርስቲያን እንዲሰጥልኝ እፈልጋለሁ ። ” ሲሉ ለቤተሰቦቻቸው ያልተናገሩትን የራስ ሚስጥርን በየዋህነት ላመኖት አገልጋይ ተከራይ ሀሳባቸውን ያካፍላሉ ።

አገልጋይ ነኝ ባዬ ይቺን ፍንጭ ትይዝና ዘወትር ምሽት ላይ “አንቺ ትሞቻለሽ ፣ የሞት ድምፅ እየሰማሁ ነው ። ” በማለት ከጌታ የተሰጠ መልዕክ ነው ። በሚል በወይዘሮ ዘንባቤ ላይ የፍራቻ ፣ የድንጋጤ ስሜትን መዝራት ትጀምራለች ። እናም እንዲህ ትላቸዋለች ያው “እኔ የእግዚያብሔር አገልጋይ ነኝ ስለዚህ ስትሞቺ ለኔ ብትሰጪኝ ለቤተክርስቲያን እንደሰጠሽ ይቆጠራል ። ” ትላቸዋለች ይሄኔ ሁሉን እውነት ነው ብለው የተቀበሉት እኚ ወይዘሮ አንዱን ቤት ሸጠው ለተከራያቸው ቅሊንጦ አካባቢ በለ አንድ ኮንዶሚኒየም በስሞ ይገዙላታል ። በተረፈው አምስት መቶ ሺ ብር ደግሞ ለእሳቸው ኮዬ ፈጬ እስቱዲዬ ይገዙና ያከራያሉ ።

See also  ፈረንሳይና አሜሪካ 8.3 ሚሊዮን ዶዝ የኮቪድ ክትባት ሰጡ

በዚህ ያላበቃው የአገልጋያቸው ጉድ” ክራይ ለመቀበል ኮዬ ድረስ ከሚሄዱ ለኔ ሙሉ ውክልና ይስጡኝና እኔ ቤቱን አስተዳድረዋለሁ ።” ብላ ሙሉ ውክልና ትወስድና ቆዬ ፈጬ የገዙትን ቤት በ150 ሺ ብር እንደተሸጠ አድርጋ አካውንታቸው ላይ እንዲገባ ታደርጋለች ።

መልሳም መረጃና ማስረጃ እንዳይኖርባት ይሄንኑ 150 ሺ ብር በካሽ ሃምሳ ሃምሳ ሺ ብር እያወጡ በእጆ እንዲሰጦት ታደርግና ወደ ራሷ አካውንት ታስገባለች ።

የሰውን ለብ እና እንባ እንደ ተራ ነገር የቆጠረችው አገልጋይ ተብዬ ወይዘሮ ዘንባቤን ባዶዎቸውን ማስቀረቷ ሳያንስ አሁን ያሉበትን ቤት በስጦታ እንዲሰጦት በማድረግ ቤቱን በስሞ አስደርጋለች ።

በአሁን ሰዓት አገልጋይ ተብዬ ሶስት በአራት በሆነችው ቤት ውስጥ እየኖረች ሲሆን ወይዘሮ ዘንባቤ ደግሞ ዋናው ቤት ላይ እየኖሩ ይገኛሉ ። ነገር ግን ቤቱ በስጦታ መልክ ለአገልጋይ ተብዬ በህጋዊ መንገድ ተሰጥቷታል።

የህግ ባለሙያዎች ይሄን ጉዳይ ከህግ አንፃር እንዴት ይታይ ይሆን ሙያዊ ሀሳባችሁን አካፍሉን ።

የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዬች ፣ ፓስተሮች ፣ መጋቢዎች ለሀይማኖታችሁ ቀናኢ የሆናችሁ በዚህ ጉዳይ ላይ ምን ትላላችሁ ?

ወዳጄ ፣ ጓደኛዬ ጋዜጠኛ አለምሰገድ ታደስ ሁሌም አስገራሚ ታሪኮችን በሬዲዬ በእርቅ ማዕድ ፕሮግራም እና በኢዬሀ ሚዲያ ዩቲዩብ ቻናል ለምታካፍለን አስተማሪ ታሪኮች አክብሮቴ ባለህበት ይድረስልኝ ።
Tariku zewdu

Leave a Reply