ምክር ቤቱ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ወይዘሮ ሌሊሴ ደሳለኝን ሹመት መርምሮ አፀደቀ
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ወይዘሮ ሌሊሴ ደሳለኝን እና ምክትል ፕሬዚዳንት ወይዘሮ ዛህራ ኡመር አሊ ሹመትን መርምሮ አፀደቀ፡፡
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በዛሬው እለት 13ኛ መደበኛ ጉባዔውን እያካሄደ ነው፡፡
ምክር ቤቱ እያካሄደ በሚገኘው 13ኛ መደበኛ ጉባዔ በዕጩነት የቀረቡ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ወይዘሮ ሌሊሴ ደሳለኝ እና ምክትል ፕሬዚዳንት ወይዘሮ ዛህራ ኡመር አሊ ሹመትን መርምሮ በአብላጫ ድምፅ አጽድቋል፡፡
FBC