በሽብር ወንጀል የተጠረጠሩ አምስት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው ፍርድ ቤት ቀረቡ


Warning: array_column() expects parameter 1 to be array, string given in /home/ethio12/www/www/wp-content/plugins/coblocks/src/blocks/posts/index.php on line 32

በአመራሮች ላይ ጥቃት ለመፈፀም እና ግድያን ለማስቀጠል ፣ ሕገ መንግስቱንና ሕገመንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለማፍረስ በማሰብ በኢ – መደበኛ አደረጃጀት በመፍጠር ሲንቀሳቀሱ ነበሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች ናቸው በቁጥጥር ስር ውለው ፍርድ ቤት የቀረቡት።

ፍርድ ቤት የቀረቡት ተጠርጣሪዎችም መንበረ አለሙ ተከታይ፣ ሲሳይ መልካሙ አበበ፣ ገብርዓብ አለሙ ዘሪሁን (ዶ/ር)፣ ተስፋዬ መኩሪያው አበባው እና ወንደሰን ተገኝ ተስፋዬ ይባላሉ።

ተጠርጣሪዎቹ ለሽብር ተግባር ሲንቀሳቀሱ መንግስት ባደረገው የሕግ ማስከበር ስራ አራቱ በአማራ ክልል በቁጥጥር ስር ሲውሉ÷ 5ኛ ተጠርጣሪ ወንደሰን ተገኝ ተስፋዬ ደግሞ በአዲስ አበባ ከተማ መያዙን የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን መርማሪ ለጊዜ ቀጠሮ ችሎት አስረድቷል።

ተጠርጣሪዎቹ የፖለቲካ ፍላጎታቸውን ለማሳካት በአመራሮች ላይ የሚያደርጉትን ግድያ ለማስቀጠል በማሰብ ፣አመፅና ብጥብጥ እንዲነሳ በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎችና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ውስጥ ለወንጀል ተግባር የሚሳተፉ ተማሪዎችን ሲያደራጁ ነበር ሲል ፖሊስ ለጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ አብራርቷል።

በተጨማሪም አንደኛና ሁለተኛ ተጠርጣሪዎች በአማራ ክልል ሕገመንግስቱን እና ሕገመንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለማፍረስ በኢ-መደበኛ አደረጃጀት ለተደራጁ ወጣቶች ስልጠና ሲሰጡ እንደነበር መርማሪ ፖሊስ አስረድቷል።

ፖሊስ በተጠርጣሪዎች ላይ በዚህ መልኩ በተጀመረባቸው የመነሻ የምርመራ ስራን አጠናክሮ ተጨማሪ ማስረጃ አካቶ ለመቅረብ በወ/መ/ስ/ህግ ቁጥር 59/1 መሰረት የ14 ቀን የምርመራ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል ።

ተጠርጣሪዎቹ በበኩላቸው÷ በፖሊስ የተገለፀው የሽብር ተግባር ተሳትፎ እንደሌላቸው በመከራከር የዋስ መብታቸው እንዲከበር ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል።

የተጠርጣሪዎችን የጊዜ ቀጠሮ መዝገብ የተመለከተው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤቱ ልደታ ምድብ 1ኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ካለው የስራ ሰዓት አኳያ ተወያይቶ ለመወሰን በሚል በይደር ቀጠሮ ሰጥቷል።

fana

የባህር ዳር ነዋሪዎች- ኢትዮጵያን ዜጎች በሁሉም ቦታ እኩል የሚስተናገዱባት ሀገር ማድረግ ይገባል
የባህር ዳር ነዋሪዎች የሕዝብን ጥያቄ የመፍታት አቅም፣ ፍላጎት እና ቅንነት ያለው አመራር በመፍጠር ሕዝብን መካስ እንደሚያስፈልግ፣ ኢትዮጵያ በዘር ከመገፋፋት እና ከመጠቃቃት ነጻ የኾነች ፣ዜጎች በሁሉም ቦታ እኩል የሚስተናገዱባት ሀገር እንድትኾን ማድረግና የፌዴራል መንግሥት የአማራ ሕዝብ ኅብረ ብሔራዊ እና ልማት ወዳድ እንጅ ጦርነትን የማይፈልግ መኾኑን በውል በመገንዘብ የሕዝቡን ተዘዋውሮ የመሥራት እና የደኅንነት መብት እንዲያስተብቅ በውይይት መድረክ …
ለወልቃይት ጠገዴ ሴቲት ሁመራ አንድ ሚሊዮን የጉልበት ሰራተኛ ይፈለጋል፤ ከአንድ ነጥን አንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ሰሊጥ ይጠበቃል
   Facebook   Twitter   Messenger   Linkedin   Pinterest "ከየትኛውም የኢትዮጵያ ክልል አስተማማኝ ሰላም ያለው እዚህ ነው። ለሰራተኞች እንደ ቤተሰብ ዝግጅት አድርገናል። ኑ" ሲሉ የተሰሙት አምስት መቶና ሶስት መቶ ሄክታር ሰሊጥና ማሽላ ያመረቱ ባለሃብቶች ናቸው። የዞኑ ግብርና ቢሮ ሃላፊ እንዳሉት አንድ ሚሊዮን አንድ መቶ ሃምሳ ሁለት ሺህ ኩንታል የሰሊጥ ምርት ስለሚጠበቅ ከአንድ ሚሊዮን በላይ የሰራተኛ ሃይል ያስፈልጋል። የዞኑ …
የጎንደርን ከተማ ምን አይነት ተኩስ እንደሌለ ተገለጸ፤ ጎንደር ተይዛለች ተብሎ ነበር
"ጎንደር ከተማን ሙሉ በሙሉ ይዘናታል" ሲሉ ስማቸው እንዳይገለጽ ጠይቀው ለጀርመን ድምጽ መረጃ በሰጡ የአማራ ሕዝባዊ ኃይል ፋኖ ቃል አቀባይ አየር ማረፊያውን ሆን ብለው እንዳልያዙ አመልክተዋል። እሳቸው ተናገሩ የተባለው በጀርመን ድምጽ እየተሰማ በለበት ሰዓት በተመሳሳይ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ውጊያ መደረጉን ሳያስተባብል ከተማዋን ለመያዝ የገባው ሃይል መደምሰሱን አሃዝ ጠቅሶ አመልክቷል። አገር መከላከያም ስም ጠቅሶ ከተደመሰሱት መካከል አመራሮች …
See also  ከ3 ሚሊየን ብር በላይ በቢሮው አስቀምጦ የተገኘው ተከሳሽ በ13 ዓመት ፅኑ እስራና በ75 ሺህ ብር አንዲቀጣ ተወሰነበት

Leave a Reply