“በአንድ ልብ፤ በአንድ ሃሳብ የተወሰነ ነው” ሲሉ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብጹዕ አቡነ ጴጥሮስ ማስታወቃቸው ተዘገበ። ቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ተቀምጦ እያለ ተከበበ፣ በወታደሮች ትጥለቀለቀ፣ ህዝብ ሁኒታውን ተከታተል፣ በግድ የማይፈለጉ ሰዎችን እንዲሾም መሳሪያ ተመዞባቸዋል ….ወዘተ በሚል ዜና ሲሰራጭ ቢውልም፣ በስተመጨረሻ ውሳኔውም ሆነ ስብሰባው በምን መልኩ እንደተካሄደ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ አመልክተዋል።
“ሁላችንም ተወያይተንበት፣ ቤተክርስቲያንን የሚጠቅማት ምንድነው? ብለን በአንድ ልብ በአንድ ሃሳብ የወሰንነው ነው። በእውነት ደስ የሚል ነበር፤ ለዚህም እግዚአብሔርን እናመሰግናለን” ሲሉ ብጹዕ አቡነ ጴጥሮስ ተናግረዋል።
አቡነ ጴጥሮስ አክለውም “ብዘዎች የተጨነቃችሁ ምዕመናን እንደነበራችሁ እናውቃለን፤ አንዳንዴ እውነት ነው፤ ብዙ ጊዜ ግን ወሬ ይበዛዋል !… በዚህ ሚዲያ በበዛበት ዘመን … ” ሲሉ ብጹዕ አቡነ ጴጥሮስ በለሆሳስ ሲሰራጭ የነበረውን ወሬና ቅስቀሳ አጣጥለዋል።
ሰፊ ቅስቀሳና ህዝብ በነቂስ ለመውጣት እንዲዘጋጅ ጥሪ የቀረበበት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዛሬው ውሎው ችግር ባለባቸው እና አስፈላጊ በሆኑባቸው አህጉረ ስብከት ዘጠኝ አዳዲስ ኤጲስ ቆጶሳት እንዲሾሙ ውሳኔ ማሳለፉ ተገልጿል። ሹመቱም ወደፊት ይፋ እንደሚሆን ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ አስታውቀዋል።
ይህ የተገለጸው የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የግንቦት 2015 ዓ/ም የርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤን በተመለከተ አጭር መግለጫ በሰጡትበት ወቅት ነው። መግለጫውን ተከትሎ የሃሰት መረጃና ጥሪ ሲያሰሙ የነበሩ አካላት ይቅርታም ሆነ ማስተካከያ ዜና አልቀረቡም።
” የግንቦት 2015 ዓ/ም የርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ በሰላም እና ደስ በሚል ሁኔታ ተጠናቋል።” ሲሉ አቡነ ጴጥሮስ ማስታወቃቸውን ተከትሎ የሚጠብቃቸው ነቀፌታና ተቃውሞ እስካሁን ለአየር ባይበቃም እንደማይቀርላቸው አካሄዱን የሚያውቁ እየገለጹ ነው።
“ዛሬ የመጨረሻው አጀንዳ ላይ ብዙ ውይይት ተካሂዷል። በመጨረሻ ሁሉም አባቶች ተወያይተው ቤተክርስቲያንን የሚጠቅመው ምንድነው ? የሚለው ላይ በመምከር ዛሬ ውሳኔ ተላልፏል።” ብለዋል።
የኤጲስ ቆጶሳት ሹመት እንዲካሄድ ተወስኗል። የመጀመሪያው ችግር ያለባቸው ሀገረ ስብከት የሚል ሲሆን አሁን ሰባት አባላት ያሉት ኮሚቴ ተቋቁሟል እነሱ በሚያቀርቡት ጥናት ሹመት ይካሄዳል። የሹመቱ ቀን ወደፊት ይገለፃል። ዋናው ነገር ለቤተክርስቲያን የሚጠቅመው የትኛው ነው ? የሚለውን የጉባኤው አባላት በሙሉ ተስማምቶ ፣ በአንድ ልብ፣ በአንድ ሃሳብ፣ በመነጋገር ውሳኔ መተላለፉን ዋና ጸሃፊው አረጋግጠዋል።
ረቡዕ የማጠቃላይ መግለጫ በቅዱስ ፓትርያኩ እንደሚሰጥ
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ተናግረዋል። “ብዙ የተጨነቃችሁ ምዕመናን እንዳላችሁ እናውቃለን፤ ምዕመናን በሙሉ ተጨንቃችኃል፤ አንዳንድ ጊዜ እውነት ነው ሌላ ጊዜ ወሬም ብዙ ይበዛል በዚህ ሚዲያ በበዛበት ዘመን በጣም ብዙ የተጨነቃችሁ ምዕመናን እንዳላችሁ እናውቃለን ፤ በእውነት እግዚአብሔርን እናመሰግናለን ግሩም የሆነ የትምህርት ጊዜ፣ ግሩም የሆነ የውይይት ጊዜ ፣ ቤተክርስቲያን ለይተን የምትፈልገው ምንድነው የሚለውን የተወያየንበት ጊዜ ነው” ሲሉም ለቤተክርስቲያኒቷ ቤተሰቦችና ዜናው ላሳሰባቸው ሁሉ የእረፍት መልዕክት አስተላልፈዋል።
አዲስ አበባ ከብልጽግና ከፍተኛ አመራሮችና የመከላከያ አዛዦች ጋር አብሮ ሲሰራ የነበረው አቶ መሳይ መኮንን “ሁለት አስቸኳይ መረጃዎች” ሲል “ቤተክርስቲያን አካባቢ ጥሩ ነገር የለም” ሲል መነግስት የስብሰባውን ውጤት ለመቀልበስ የኦሮሚያ ብልጽግና የፖሊስና የደህንነት ሃይል ማሰማራቱን አመልክቶ ነበር።
በሌላ መረጃ ከሲኖዶስ ስብሰባ ጋር ያለው ግንኙነት ግልስ ባይደረገም የኦነግ ሰራዊት ከተሞችን እየተቆጣጠረ ግምቱን አስቀምጦ መረጃ አሰራጭቶ ነበር።
ዋሱ በቴሌግራም ገጹ ፎቶ አስደግፎ ” ቅዱስ ሲኖዶሱ ስብሰባ ላይ መሆኑ ይታወቃል።ፎቶው ሲነሳ ቀንና ሰዓት ይመዘግባል። እኔ አሁን ስብሰባው በሚካሄድበት በር ላይ እያለፍኩ ነው።የፀጥታ ሀይሎች ሲርመሰመሱ ያየሁበት ነገር የለም።ከፍ ብሎ አንዲት የፌደራል ፖሊስ ፓትሮል ተመልክቻለሁ።ያለው ነገር ይሄ ነው።ሠላምን እንመኝ።መልካም ነገሮችን ያብዛልን ለማለት ነው” ሲል ምስክርነቱን ሰጥቷል።
የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሃፊ እውነቱን ካስታወቁ በሁዋላ አንዳችም ማስተባበያ ይህ እስከታተመ ድረስ አልተሰማም።
ይህን አስመልክቶ አስተያየት የሰጡ ” ውሸት የተለመደ ነው። ውሸታም ሚዲያን ሁለተኛ አላድምጥም የሚልም የለም። በሰበር መረጃ ሃሰት ሲረጭ የሚቀበሉ ሃሰቱ ሲገለጽ ለምን እንደተዋሸ የሚመረምሩ አለመኖራቸው፣ እንዲያውም በማህበራዊ ሚዲያው ሰፈር ውሸታሞችን የሚያምኑ መበራከታቸው አሳሳቢ ነው”
- ቀሲስ በላይ ከ 6.5 ሚሊዮን ዶላር በላይ ህገወጥ የገንዘብ ዝውውር ወንጀል ታስረው ፍርድ ቤት ቀረቡMore stories ዝናሽ ታያቸው – ስኬታማዋ ቀዳማዊ እመቤትOctober 16, 2021 እነ ዶክተር አሸብር በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋሉ፤ ደራርቱ የተቃውሞ ሰልፍ አደረገችMarch 29, 2021 የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የወለጋ ጉዞ ምን ይናገራል?April 21, 2023 ራያ አላማጣ – “በወረዳው በአማራ ታጣቂዎች ሰር የነበሩት ሁለት ቀበሌዎች ነፃ ወጥተዋል”April 16, 2024 ቀሲስ በላይ ከስድስት ሚሊዮን አምስት መቶ ሺህ ዶላር… Read more: ቀሲስ በላይ ከ 6.5 ሚሊዮን ዶላር በላይ ህገወጥ የገንዘብ ዝውውር ወንጀል ታስረው ፍርድ ቤት ቀረቡ
- “ንገሩዋቸው፣ ምከሩዋቸው” ሌላ ጦርነት እብደትሰሞኑንን ለይቶለት ይፋ ሆነ እንጂ ውስጥ ውስጡን የጦርነት እንቅስቃሴ ሲደረግ እንደነበር መረጃዎች ከበቂ በላይ ነበሩ። ለዚህም ይመስላል ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ” ንገሩዋቸው፣ ምክሩዋቸው” ሲሉ ከትግራይ ህዝብ ተወክለው ከመጡ ጋር ሲወያዩ ደጋግመው ያስታወቁት። በወይይቱ ላይ የተገኙ እናቶችም ” ካሁን በሁዋላ” ሲሉ ጦርነቱ ያስከተለው መዘዝና ጠባሳ እያንዘፈዘፋቸው ” ልጆቻችንን አንሰጥም” ሲሉ የተሰሙት። የድንበርና የማንነት ውዝግብ ያልተለየው የአማራና… Read more: “ንገሩዋቸው፣ ምከሩዋቸው” ሌላ ጦርነት እብደት
- የባህር ወንበዴ ሲሳዮች – በገሃነም የሚመሰለው ስቃይየ34 ዓመቱ ኢትዮጵያዊ ከአውሮፕላኑ ሲወርድ እግሮቹ ቆስለው መራመድም ሆነ መቆም አቅተውታል። ብርክ ይዞት ይንገዳገዳል፡፡ ይህ ሰው የተሻለ ህይወት ይኖረናል ብለው በሕገ ወጥ መንገድ ወደ ሳኡዲ ዓረቢያ በባህር ላይ ተጉዘው ለእንግልት ከተዳረጉ ዜጎች መካከል አንዱ ነው፡፡ አብዱረሃማን ከማል ይባላል፡፡ ምስራቅ ሀረርጌ ባበሌ የትውልድ ሥፍራው ናት፡፡ በሱማሊያና በየመን አድርገን ወደ ሳኡዲ ዓረቢያ ለመግባት ሲሞክር አሲር በሚባል የሳኡዲ… Read more: የባህር ወንበዴ ሲሳዮች – በገሃነም የሚመሰለው ስቃይ
- ትህነግ ለአራተኛ ጊዜ የአማራ ህዝብ ላይ ወረራ በመፈጸሙ አማራ ክልል ህዝቡን ለመከላከል እንደሚገደድ አስታወቀ፤ ፌደራል መንግስት ጥያቄ ቀርቦለታል“ህወሓትና የግብረ አበሮቹ ፖለቲካዊ ግልሙትና እና ደም አፋሳሽ ጦርነት ለማድረግ ከመሞከር እንዲታቀቡ ይገባል” ሲል አማራ ክልል አሳሰበ። ስም ጠቅሶ ለአራተኛ ጊዜ ወረር የተፈጸመባቸውን ስፍራዎች አስታወቀ። መላው የኢትዮጵያ ህዝብ፣ የፌደራል መንግስትና ዓለም ዓቀፍ ማህበረሰብ የህወሃትን የዳግም የጦርነት አዋጅ እንዲያወግዙና እንዲያስታግሱ ጠይቋል። ትህነግ ወረራ የፈፀመባቸው የራያ አላማጣ፣ ራያ ባላ፣ ኦፍላ፣ ኮረም እና ዛታ እንደሆኑ ያስታወቀው መግለጫው የክልሉ… Read more: ትህነግ ለአራተኛ ጊዜ የአማራ ህዝብ ላይ ወረራ በመፈጸሙ አማራ ክልል ህዝቡን ለመከላከል እንደሚገደድ አስታወቀ፤ ፌደራል መንግስት ጥያቄ ቀርቦለታል
- የራያ አላማጣ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሞላ ደርበው ሲገደሉ ሌሎች ሃላፊዎች ሸሽተዋል፣ ግድያውን ማን ፈጸመው?የራያ አላማጣ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሞላ ደርበው መገደላቸውን እና ሌሎች የወረዳው እና የከተማዋ ኃላፊዎች አካባቢውን ለቅቀው ወደ ሌሎች የራያ ወረዳዎች መሸሻቸው ተሰማ። ገዳያቸውን ለመግለጽ ፈቃደኛ እንዳልሆኑ ዜናውን ይፋ ያደረጉት ሃላፊ ገልፀዋል። የትግራይ ሃይሎች ከአላማጣ ከተማ በሶስት ኪሎሜትር ርቀት ላይ እንደሚገኙ ቢገለጽም ቢቢሲ ያነጋገራቸው የከተማዋ ከንቲባ አቶ ኃይሉ አበራ “ካለፈው ሳምንት ቅዳሜ ጀምሮ የተኩስ ልውውጥ… Read more: የራያ አላማጣ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሞላ ደርበው ሲገደሉ ሌሎች ሃላፊዎች ሸሽተዋል፣ ግድያውን ማን ፈጸመው?