ከሳምንት በፊት “ኢትዮጵያ አራተኛውን ዙር የውኃ ሙሌት በቅርቡ ትጀምራለች፤ አሁንም አቤቱታችሁን ወደ ጸጥታው ምክር ቤት ልትወስዱት ትችላላችሁ?” የሚል ጥያቄ በጋዜጠኞች የቀረበላቸው የግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሚ ሽኩሪ የሰጡት ምላሽ የአረብ ሊግ የአቋም መግለጫን ቀድሞ ያመላከተ ነበር፡፡ “ከፈረሱ ጋሪው ቀደመ” እንደሚባለው ከስብሰባው በፊት የአቋም መግለጫውን የስብሰባው ዘዋሪዎች ለዓለም ሕዝብ ጆሮ አደረሱት፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ሳሚ ሽኩሪ በምላሻቸው “እስከአሁን አቤቱታችንን ከጸጥታው ምክር ቤት እስከ አፍሪካ ኅብረት አቅርበን የተለየ ነገር አልመጣም፡፡ በተደጋጋሚ መንገድ መሄድ ሳይኾን ጉዳዩን አቅጣጫ ቀይሮ መመልከት ተገቢ ነው፡፡ የግድቡን የውኃ ሙሌት በተመለከተ ግብጽ ጉዳዩን ወደ አረብ ሊግ ትወስደዋለች” ሲሉ ተደመጡ፡፡ እንደ እውነቱ ከኾነ በሳዑዲ አረቢያ ጅዳ የተካሄደው 32ኛው የአረብ ሊግ ስብሰባ ከወትሮው የተለየ እና ትኩረት የሚሹ የመወያያ አንገብጋቢ ነጥቦች ነበሩት፡፡
የአረብ ሊግ እንደ አውሮፓዊያኑ የዘመን ቀመር መጋቢት 22/1945 ሲመሰረት ከመሥራቾቹ ሰባት ሀገራት መካከል አንዷ የኾነችው የበሽር አላሳዷ ሀገር ሶሪያ ከ12 ዓመታት በኋላ በተመለሰችበት ስብሰባ ከኢትዮጵያ የተሻገረ የአባል ሀገራቱ አንገብጋቢ ጉዳዮች ነበሩባቸው፡፡ የሱዳን የእርስ በእርስ ጦርነት እና በጦርነት የተጎዳችውን ሶሪያን ከማቋቋም በላይ በሕዳሴ ግድቡ ዙሪያ አቋም መያዝ ከሊጉ ጀርባ የስብሰባው ዘዋሪዎች እነማን እንደነበሩ በግልጽ አመላካች ኾኖ ታይቷል፡፡
ላለፉት ሦስት ዓመታት በሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት ዙሪያ ከካይሮ ጋር የወገነችው ካርቱም በሁለቱ ጀኔራሎቿ እልኽ አስጨራሽ ጦርነት ድምጿ ጠፍቷል፡፡ በጦርነቱ ዋዜማ እንዴት እና ለምን ሱዳን ውስጥ እንደተገኙ እስካሁንም ድረስ ምክንያቱ ግልጽ ያልኾነው የግብጽ ወታደሮች ጉዳይ ለሱዳን ሕዝብ የእግር እሳት በኾነበት በዚህ ወቅት ግብጽ በውኃ ሙሌቱ ዙሪያ ሱዳንም ተመሳሳይ አቤቱታ እንዳላት ሳዑዲ አረቢያ ጅዳ ተገኝታ ጉዳይ ፈጻሚ መኾኗን አረጋገጠች፡፡ ይህ ሁሉ ተሰባስቦ የዓባይ ጉዳይ ከግብጽ እስከ አረብ ሊግ ውስብስብ እጆች እንዳረፉበት አመላካች ነው ይላሉ የታሪክ ምሁሩ ፕሮፌሰር አደም ካሚል፡፡
ግንባር ቀደም ጉዳይ አስፈጻሚዎቹ እና ዋና ጽሕፈት ቤቱ ካይሮ ላይ ከተቀመጠ ሊግ ከዚህ የተለየ አቋም መጠበቅ “በተኩላ ዘመን በግ መኾን” ነው ያሉት ፕሮፌሰር አደም ሳዑዲ አረቢያም የዓባይን ጉዳይ የአረቡ ዓለም ጉዳይ ለማድረግ በቅርቡ የምታደርጋቸው እንቅስቃሴዎች የሊጉ አቋም ቅድመ ምልክቶች ነበሩ ይላሉ፡፡ በሳዑዲ አረቢያው የሊጉ ስብሰባ የሕዳሴ ግድቡን በሚመለከት የታየው አቋም ከወትሮው ያልተለየ እና መሻሻል ያልታየበት ነውም ብለዋል፡፡
“የግብጽ የውኃ አቅርቦት ጉዳይ የአረብ ሊግ ሀገራት የፀጥታ ስጋት ጉዳይ ነው” የሚለው የሊጉ ወቅታዊ አቋም የሳዑዲ አረቢያን ፍላጎት ታሳቢ ያደረገ ነው የሚሉት ፕሮፌሰር አደም ምክንያቱን ሲያነሱም ሳዑዲ አረቢያ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በግብጽ እና ሱዳን ከፍተኛ የእርሻ ኢንቨስትመንት ማስፋፋቷን ተከትሎ የቀረበ ስጋት ነው ይላሉ፡፡ ኢትዮጵያ በየጊዜው “አልቀበለውም” ከሚል ምላሽ ወጥታ ዲፕሎማሲያዊ ሥራዎችን በጥናት እና በውጤት ተመስርታ መሥራት እንደሚኖርባትም አስገንዝበዋል፡፡ በተጨማሪም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየጎላ የመጣው የፐብሊክ እና ዲጂታል ዲፕሎማሲ ለግብጽ ሴራ ፍቱን መድኃኒት እንደኾነም አንስተዋል፡፡
ዘጋቢ፡- ታዘብ አራጋው ባሕር ዳር ፡ (አሚኮ)
- “ደብረ ኤሊያስ ገዳም የደረሰበት ጉዳት የለም” ወረዳው፤ መከላከያ ስራውን መጨረሱ ተሰማአካባባዊ በተለይም ገዳሙ ወታደራዊ ማስለጠኛ፣ የሚፈለጉ ሰዎች መመሸጊያ፣ ሃይማኖታዊ ዓላማውን የሳተ በመሆኑ በአባቶች፣ በሃይማኖት መሪዎች፣ በመንግስት ሃላፊዎችና ታውቃ ሰዎች ቢለመኑም ፈቃደኛ እንዳልሆኑ፣ በስተመጨረሻም ደብሩም ሆነ መኖኮሳቶች ምንም ሳይሆኑ መከላከያ ገብቶ ስራውን አከናውኖ መጨረሱ ተሰማ። በርካታ ታጣቂዎች ለመከላከያ እጃቸውን መስጠታቸውም ተገልጿል። ወረዳው መከላከያ ስራውን ጉዳት ሳያደርስ ማከናወኑን ይፋ ሲያደርግ እጅቻውን ስለሰጡናContinue Reading
- አሮጌውን ወይን በአዲስ አቁማዳ ! የኖርንበት ፣ የቸከ የሰለቸ የፖለቲካ …የኢትዮጵያ ታሪክ የእርስ በእርስ ጦርነት civil war & strife ነው። ይሄንን ያደፈ ጉድለታችንን ማስተካከል የምንችለው መሀከለኛውን መንገድ የያዙ ስብስቦችን በማብዛት ነው። ችግሩ በእኛ ሀገር ፖለቲካ መሀከሉን መንገድ ልትይዝ ስትሞክር የሚወረወርብህ ፍላጻ መብዛቱ ነው። ለዚህ ጥሩ ምሳሌ ኢዜማ ነው። ህወሃትም ፣ የኦሮሞ ብሄረተኜችም ፣ በቅርብ የተፈለፈሉት የአማራ ብሄረተኞችም ለፓርቲው ያላቸውን ጥላቻContinue Reading
- US Special Envoy for HoA Amb Mike Hammer to Visit EthiopiaUS Special Envoy for the Horn of Africa Ambassador Mike Hammer will visit Ethiopia on May 31 – June 6. In Ethiopia, Ambassador Hammer will meet African Union officials on implementation of the November 2, 2022 Cessation of Hostilities Agreement (COHA). He will discuss progress and priorities including transitional justiceContinue Reading
- በሽብር ወንጀል በተጠረጠሩ በ38 ግለሰቦች ላይ ተጨማሪ የ14 ቀን ጊዜ ተፈቀደየፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት በ3 መዝገብ የቀረቡ የ38 ተጠርጣሪዎችን ጉዳይ ተመልክቷል። ተጠርጣሪዎቹን ፍርድ ቤት ያቀረበው የፌደራል ፖሊስ መርማሪ በቀዳሚነት በነመላክ ምሳሌ መንግስቱ መዝገብ የተካተቱ 16 ግለሰቦችን እና በነደበበ በሻህ ውረድ መዝገብ የተካተቱ በ12 ተጠርጣሪዎች አጠቃላይ 26 ግለሰቦች ላይ የሽብር ወንጀል የጥርጣሬ መነሻውን በፅሁፍም በቃልምContinue Reading
- ሟችን በጭፈራ የሚሸኘው ማህበረሰንበደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በኮንሶ ዞን ውስጥ ተወልደው ያደጉት ዶ/ር ኦንጋዬ ኦዳታ በቅርቡ ነው አያታቸውን በሞት ያጡት። የሚወዷቸው አያታቸው ቀብር የተፈፀመው ግን ወዳጅ ዘመድ ተሰብስቦ ዘፍኖ እና ጨፍሮ በተከናወነ ሥነ ሥርዓነት መሆኑን ከቢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል። ሞት በሁሉም ዘንድ ሁሌም አዲስ ነው። በመጣ ቁጥር የሚያስደነግጥ በብዙ ማኅበረሰቦች ዘንድም ማቅ የሚያስለብስContinue Reading