ዘመድኩናዊነትን ያሸነፉ አባት !

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን በቅርብ ጊዜ የወረራት ፣ የተጣባት ቫይረስ ዘመድኩናዊነት ይባላል። ዘመድኩናዊነት እንደ ቀደመው ዘመን ፈሪሳዊነት 99.9% ጊዜውን የሚያጠፋው የእግዜሩን ቃል በማካፈል ፣ ቀን የጎደለባቸውን ደገፍ ማድረግ ላይ አይደለም። ዘመድኩናዊነት አሳዳጅነት ፣ ስድነት ፣ ተሳዳቢነት ነውርን ክብር አድርጎ አደባባይ የመውጣት ህመም ነው።

ዘመድኩናዊነት ባይኖር ኖሮ ዛሬ እነ መምህር በጋሻው አጠፉ ለሚባሉት ይቅርታ ጠይቀው ቤተክርስትያኒቱን አማኙን ባገለገሉ ነበር። ዘመድኩናዊነት ባይገን ኑሮ ዛሬ መነኩሴው ፣ ዘማሪው ፣ ሰባኪው ውሎውን ቲክቶክ ፣ ፌስቡክና ዩቱይብ ላይ ባላደረገ ነበር። ዘመድኩናዊነት በጓዳ የሰማኸውን የጓደኛህን ህጸጽ በአደባባይ በሞንታርቦ ለህዝብ የማወጅ ነውረኝነት ነው።

አቡነ ጴጥሮስ ክርስትናን ሊኖሩት የሚሞክሩ ፣ የሚታትሩ ክህን ናቸው ስል አስባለሁ ። አቡነ ጴጥሮስ እና ካህናት ወዳጆቻቸው እነ አቡነ ሳዊሮስን ረግሞና አዋርዶ ከቤተስኪያን ከማራቅ ይልቅ ይቅርታን ፣ ክርስትያናዊ ወንድማማችነትን ለምዕመኑ ያስተማሩ ይመስለኛል። አቡነ ጴጥሮስ በትናንትናው ንግግራቸው የማህበራዊ ሚዲያን አጥፊነትን በገደምዳሜም ጠቆም አድርገዋል ። የዚህ ዘመን ምዕመን መንፈሱ ለዘመድኩናዊነት ቅርብ ነው ፣ ትናንት አባ ያላቸውን ካህናት ዛሬ በመንደር ቃል ለመዘርጠጥ ሰከንዶች አያመነታም። ብዙው አማኝ የእግዜሩን ቃል ከማዳመጥ ፣ በየሰፈሩ ቀን ለጎደለባቸው የሚላስ የሚቀመስ ከማካፈል የቤተስኪያን ጠላቶች የሚላቸውን ቢያሳድድ ለአምላኩ ትልቅ ውለታ የሚውል የሚመስለው ነው።

ክርስትና ሌሎችን መውደድ ፣ ደከም ያሉትን ( በመንፈስም በስጋም ) ማገዝ ነው። ክርስትና ውስጡ የአሳዳጅነትና ከሳሽነት መንፈስ ፍጹም የለበትም። አቡነ ጴጥሮስ ውስጥ ፍቅርና ትህትና የሞላበት ክርስትናን አያለሁ ።

መምሬ Samson Michailovich እንደጻፉት !

  • “ደብረ ኤሊያስ ገዳም የደረሰበት ጉዳት የለም” ወረዳው፤ መከላከያ ስራውን መጨረሱ ተሰማ
    አካባባዊ በተለይም ገዳሙ ወታደራዊ ማስለጠኛ፣ የሚፈለጉ ሰዎች መመሸጊያ፣ ሃይማኖታዊ ዓላማውን የሳተ በመሆኑ በአባቶች፣ በሃይማኖት መሪዎች፣ በመንግስት ሃላፊዎችና ታውቃ ሰዎች ቢለመኑም ፈቃደኛ እንዳልሆኑ፣ በስተመጨረሻም ደብሩም ሆነ መኖኮሳቶች ምንም ሳይሆኑ መከላከያ ገብቶ ስራውን አከናውኖ መጨረሱ ተሰማ። በርካታ ታጣቂዎች ለመከላከያ እጃቸውን መስጠታቸውም ተገልጿል። ወረዳው መከላከያ ስራውን ጉዳት ሳያደርስ ማከናወኑን ይፋ ሲያደርግ እጅቻውን ስለሰጡናContinue Reading
  • አሮጌውን ወይን በአዲስ አቁማዳ ! የኖርንበት ፣ የቸከ የሰለቸ የፖለቲካ …
    የኢትዮጵያ ታሪክ የእርስ በእርስ ጦርነት civil war & strife ነው። ይሄንን ያደፈ ጉድለታችንን ማስተካከል የምንችለው መሀከለኛውን መንገድ የያዙ ስብስቦችን በማብዛት ነው። ችግሩ በእኛ ሀገር ፖለቲካ መሀከሉን መንገድ ልትይዝ ስትሞክር የሚወረወርብህ ፍላጻ መብዛቱ ነው። ለዚህ ጥሩ ምሳሌ ኢዜማ ነው። ህወሃትም ፣ የኦሮሞ ብሄረተኜችም ፣ በቅርብ የተፈለፈሉት የአማራ ብሄረተኞችም ለፓርቲው ያላቸውን ጥላቻContinue Reading
  • US Special Envoy for HoA Amb Mike Hammer to Visit Ethiopia
     US Special Envoy for the Horn of Africa Ambassador Mike Hammer will visit Ethiopia on May 31 – June 6. In Ethiopia, Ambassador Hammer will meet African Union officials on implementation of the November 2, 2022 Cessation of Hostilities Agreement (COHA). He will discuss progress and priorities including transitional justiceContinue Reading
  • በሽብር ወንጀል በተጠረጠሩ በ38 ግለሰቦች ላይ ተጨማሪ የ14 ቀን ጊዜ ተፈቀደ
    የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት በ3 መዝገብ የቀረቡ የ38 ተጠርጣሪዎችን ጉዳይ ተመልክቷል። ተጠርጣሪዎቹን ፍርድ ቤት ያቀረበው የፌደራል ፖሊስ መርማሪ በቀዳሚነት በነመላክ ምሳሌ መንግስቱ መዝገብ የተካተቱ 16 ግለሰቦችን እና በነደበበ በሻህ ውረድ መዝገብ የተካተቱ በ12 ተጠርጣሪዎች አጠቃላይ 26 ግለሰቦች ላይ የሽብር ወንጀል የጥርጣሬ መነሻውን በፅሁፍም በቃልምContinue Reading
  • ሟችን በጭፈራ የሚሸኘው ማህበረሰን
    በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በኮንሶ ዞን ውስጥ ተወልደው ያደጉት ዶ/ር ኦንጋዬ ኦዳታ በቅርቡ ነው አያታቸውን በሞት ያጡት። የሚወዷቸው አያታቸው ቀብር የተፈፀመው ግን ወዳጅ ዘመድ ተሰብስቦ ዘፍኖ እና ጨፍሮ በተከናወነ ሥነ ሥርዓነት መሆኑን ከቢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል። ሞት በሁሉም ዘንድ ሁሌም አዲስ ነው። በመጣ ቁጥር የሚያስደነግጥ በብዙ ማኅበረሰቦች ዘንድም ማቅ የሚያስለብስContinue Reading
See also  የኢዜማ ነገር !

Leave a Reply